የኢትዮጵያ ሰራዊት ከሶማሊያ መዉጣቱ አያነጋግርም6 ታኅሣሥ 2001ሰኞ፣ ታኅሣሥ 6 2001የወታደሮቹን መዉጣት ተከትሎ በአገሪቱ ሊፈጥር የሚችለዉ የፀጥታ ክፍተት አነጋጋሪ ሆኗል።https://p.dw.com/p/GGa3የኢትዮጵያ ወታደሮች መቃዲሾምስል APማስታወቂያሰሞኑን የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮቼን ከሶማሊያ ምድር አስወጣለሁ ማለቱን ተከትሎ ሶማሊያ በተለያዩ ችግሮች መዋከቧን ቀጥላለች። የወታደሮቹን መዉጣት ተከትሎ በአገሪቱ ሊፈጥር የሚችለዉ የፀጥታ ክፍተት እንዳለ ሆኖ ባልፀናዉ የሶማሊያ የሽግግር መንግስት በከፍተኛ ስልጣን ላይ የሚገኙ ወገኖች ኃይላቸዉን በማጠናከር ፈንታ ወደዉዝግብ ዉስጥ የገቡበት ሁኔታ እየታየ ነዉ።