1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና የህግ ባለሙያ አስተያየት

ማክሰኞ፣ ሰኔ 15 2002

የምርጫ ቦርድ ኢህአዲግ የ4ኛው ዙር ብሄራዊ ምርጫ አሸናፊ መሆኑን ገለጸ። ተቃዋሚዎች ለሰበር ችሎት አቤት ይላሉ።

https://p.dw.com/p/O04n
የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ውድቅ ያደረጉት የምርጫ ውጤትምስል DW

ሰበር ሰሚ ችሎት የህግ ግድፈት ከተፈጸመ የማየት እንጂ የምርጫ ውጤቱን በተመለከተ ውሳኔ የመስጠት ሥልጣን እንደሌለው አንድ የህግና የፖለቲካ ምሁር ገለጹ። ምሁሩ ዶክተር ለማ ይፍራሸዋ እንደገለጹት ተቃዋሚዎች ሰላማዊ የሆነ አማራጮች አሏቸው። ህገመንግስቱ በሚፈቅድላቸው መሰረት በሰላማዊ ሰልፍ ተቃውሟቸውን መግለጽ ይችላሉ ብለዋል። ዶክተር ለማ የምርጫ ቦርድ የመጨረሻ ውጤትን ይዘው የፍትህ ሂደቱ እስከሚወስዳቸው ጥግ ድረስ ተቃዋሚዎቹ ሊገፉ እንደሚገባም ገልጸዋል።

መሳይ መኮንን

አርያም ተክሌ