1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 21 2008

የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሪዮ ኦሎምፒክ ዝቅተኛ ውጤት ካስመዘገበ በኋላ የኢትዮጵያ አትሌቲክ ፌዴሬሽን እና በአትሌት ኃይሌ ገብረ-ስላሴ የሚመራው የአትሌቶች ጊዜያዊ ኮሚቴ እሰጥ አገባ ላይ ናቸው።

https://p.dw.com/p/1Jr4T
Äthiopien PK olympische Athleten
ምስል DW/Getachew Tedla Haile-Giorgis

[No title]

አትሌት ኃይሌ ገብረ-ስላሴ፣ገዛኽኝ አበራ፣ ገ/እግዚአብሔር ገ/ማርያም፤ አሰለፈች መርጊያ፣ አሰልጣኝ ሻምበል ቶሎሳ ቆቱን ያካተተው ጊዜያዊ ኮሚቴ በሪዮ በተመዘገበው ዝቅተኛ ውጤት ምክንያት የኢትዮጵያ አትሌቲክ ፌዴሬሽን ስልጣኑን እንዲያስረክብ ጠይቋል። ፌዴሬሽኑ በበኩሉ አትሌቶቹ እና አመራሩ በመዋከቡ ውጤት ማምጣት አልተቻለም የሚል ምክንያት አቅርቧል። የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ አለባቸው ንጉሴ "የስልጣን ጊዜያችን ህዳር 24 ነው የሚጠናቀቀው።እስከ ህዳር 24 ሳንጠብቅ መስከረም ወይም ጥቅምት ውስጥ ጠቅላላ ጉባዔ እንጠራለን።" ብለው ተናግረዋል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

እሸቴ በቀለ

ነጋሽ መሐመድ