1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ጉባዔ

ሰኞ፣ ጥቅምት 22 2003

የሲኖዶስ አባላት፣ በቦሌ ደብረ-ሳሌም መድኃኔ-ዓለም የቆመው የአባ ፓውሎስ ሀውልትም ሆነ በየአድባራቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተሠቀሉ ፎቶግራፎች ተነስተው በመዘክር እንዲቀመጡ ውሳኔ አስተላልፏል።

https://p.dw.com/p/PvgH
መንበረ ፓትርያርክምስል DW

ከአዲስ አባባ፤ ታደሰ እንግዳው በላከልን ዘገባ ላይ እንደገለጠው፣ የኢትጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ውን ጉባዔ ሲያጠናቅቅ፣ ባወጣው መግለጫ ፣ በቤተ-ክርስቲያኒቱ በንሠራፋው ምዝበራና ሙስና ሳቢያ፣ ከፍተኛ የገንዘብ ጉድለት መገነቱ በሂሳብ መርማሪ በኩል መረጋገጡ ታውቋል። ባለፉት 3 ዓመታት በቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ ሙስናዊ አሠራር ተንሠራፍቷል፣ በአባ ፓውሎስ ዙሪያ በተሰባሰቡ ግለሰቦች አማካኝነት ከሲኖዶስ እውቅና ውጪ፣ አምባገነናዊ አሠራር ታይቷል በማለት የተቹት የሲኖዶስ አባላት፣ በቦሌ ደብረ-ሳሌም መድኃኔ-ዓለም የቆመው የአባ ፓውሎስ ሀውልትም ሆነ በየአድባራቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተሠቀሉ ፎቶግራፎች ተነስተው በመዘክር እንዲቀመጡ ውሳኔ አስተላልፏል።

ታደሰ እንግዳዉ

ተክሌ የኋላ

ነጋሽ መሐመድ