የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሲኖዶስ ጉባኤ
ረቡዕ፣ ግንቦት 10 2003ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ጠቅላይ ሲኖዶስ መደበኛ ጉባኤ አዲስ አበባ ዉስጥ በዝግ እየተነጋገረ ነዉ።የጉባኤዉን ይዘትና ሒደት የሚያዉቁ ምንጮች እንደሚሉት የቤተ-ክርስቲያኒቱ አስተዳደር ጉባኤተኞችን አሁንም እያወዛገበ ነዉ።ደቡብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በደል ደርሶብናል የሚሉ የሐይማኖቱ ተጠሪዎችና ምዕመናን ደግሞ ለጉባኤዉ አቤቱታ ለማቅረብ ወደ አዲስ አባባ መጓዛቸዉ ተሰምቶ ነበር።ይሁንና ከአቤት ባዮቹ ገሚሱ አዲስ አበባ እንዳይገቡ መታገዳቸዉ ተወርቷል።ሒሩት መለሰ የአዲስ አባባ ወኪላችንን ታደሰ እንግዳዉን አነጋግራዋለች።
ታደሰ እንግዳዉ
ነጋሽ መሐመድ
ሒሩት መለሰ