1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ የሠብአዊ መብት ይዞታና የመድረክ ወቀሳ

ማክሰኞ፣ ግንቦት 7 2004

መድረክ ባሠራጨዉ ፅሑፍ እንዳለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚገደሉ፥ የሚታሰሩና እንዲሰደዱ የሚገደዱት ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነዉ።መድረክ እንደሚለዉ መንግሥት ባለሥልጣናቱ በተቃዋሚዎች ላይ የሚያደርሱትን ግፍና በደል እንኳን አላስቆመም።

https://p.dw.com/p/14w7N
***Für mögliche Ergänzungen der Karte, wie z.B. andere Sprachen, zusätzliche Orte oder Markierungskreuz, wenden Sie sich bitte an infografik@dw-world.de (-2566), Außerhalb der Bürozeiten an bilder@dw-world.de (-2555).*** DW-Grafik: Per Sander 2011_03_10_Laender_Prio_A_B


የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናቱ በዜጎች ላይ የሚያደርሱትን በደልና የመብት ጥሰት አይከታተልም በማለት ዋነኛዉ የመንግሥት ተቃዋሚ ፓርቲ ወቀሰ።የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) ሰሞኑን ባሠራጨዉ ፅሑፍ እንዳለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የሚገደሉ፥ የሚታሰሩና እንዲሰደዱ የሚገደዱት ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነዉ።መድረክ እንደሚለዉ ለዜጎች ጥበቃ ማድረግ የሚገባዉ መንግሥት ጥበቃ ሊያደርግ ቀርቶ በተገላቢጦሹ ባለሥልጣናቱ በተለይ በተቃዋሚዎች ላይ የሚያደርሱትን ግፍና በደል እንኳን አላስቆመም።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ የመድረክን ፕሬዝዳት ዶክተር ሞጋ ፍሪሳንና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሐላፊ አምባሳደር ጥሩነሕ ዜናን አነጋግሮ የላከልን ዘገባ አለ።

ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ