የኢትዮጽያ ደራስያን ማህበር የ50ኛ አመት አከባበር
እሑድ፣ ሚያዝያ 24 2002ማስታወቂያ
የኢትዮጽያ የደራስያን ማህበር ከተመሰረተ ሃምሳኛ አመቱን ሲያከብር በተለይ ምስራቅ ጎጃም ዞንን የምትወክለዉ ደብረማርቆስን አንጋፋ ወጣት ደራሲዎችን በማፍለቅዋ በቦታዉ ሄዶ ሃምሳኛ አመቱን እንዲያከብር መነሻ ሆኖታል። ሌላዊ የአርቲስት ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ የህይወት ታሪክን ያዘለዉ መጽሃፍም ማህበሩ ግማሽ ምእተ አመቱን ሲያከብር ጽፎ ለአንባብያን እጅ ማድረሱም የልደቱን ድግስ ልዩ እንዳደረገዉ ይገልጻል። የለቱ የባህል መድረክ ዝግጅታችን የኢትዮጽያ ደራስያን ማህበር የሃምሳኛ አመት አከባበር እና የዶክተር ጥላሁን ገሰሰን የህይወት ታሪክ ያዘለዉን መጽሃፍ ያስቃኛል ለጥንቅሩ አዜብ ታደሰ ነኝ ያድምጡ! መልካም ቆይታ!
አዜብ ታደሰ፣ ተክሌ የኋላ