1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢጣልያ ምርጫ

ሰኞ፣ የካቲት 18 2005

የሮም ኤጣልያው ዘጋቢያችን ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ለኢጣልያ 630 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችና ለ 315 የህግ መወሰኛ ምክር ቤት መቀመጫዎች የተካሄደው ምርጫ ውጤት ይህ ሊሆን ይችላል ብሎ ከወዲሁ ለመገመት አስቸጋሪ ነው ይላል

https://p.dw.com/p/17ld6
ምስል picture alliance/dpa

ከጥቂት ሰዓታት በፊት የተጠናቀቀው የኢጣልያ ምርጫ ውጤት አጓጓ ሆኗል ። የምርጫ

ጣቢያዎች ከተዘጉ በኋላ የወጡ ዘገባዎች የፕየር ሉጂ ቤራሳኒ የመሃል ግራ ጥምረት

የአወዛጋቢውን የሲልቭዮ ቤርሉስኮኒን የመሃል ቀኝ ፓርቲ እየመራ መሆኑን

ይጠቁማሉ ። ይሁንና የሮም ኤጣልያው ዘጋቢያችን ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ ለኢጣልያ

630 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችና ለ 315 የህግ መወሰኛ ምክር ቤት

መቀመጫዎች የተካሄደው ምርጫ ውጤት ይህ ሊሆን ይችላል ብሎ ከወዲሁ ለመገመት

አስቸጋሪ ነው ይላል ። ተክለ እዝጊን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬው ነበር ።

ተክለ እዝጊ ገብረ እየሱስ
ሂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ