1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኤቦላ ወረርሽኝ በዩጋንዳ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 24 2004

ምእራብ ዩጋንዳ ውስጥ በፍጥነት በሚዛመተው ኤቦላ በተባለው በሽታ እንደተያዙ የሚጠረጠሩ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሄዱን መንግሥት አስታወቀ ። የበሽታውን ስርጭት የሚከታተሉ ተመራማሪዎች የኤቦላ ወረረሽኝ በአካባቢው መከሰቱን ካረጋገጡ ከጥቂት ቀናት በኋላ

https://p.dw.com/p/15hLx
A nurse and relative of Joshua Kule (R), the senior clinical officer of Bityo hospital in Bundibugyo, takes care of him at a special ward of the hospital 03 December 2007. Bityo is suspected of having contracted the lethal Ebola virus. Three people with suspected Ebola were admitted 03 December 2007 at the hospital in western Uganda, where the virus has killed 20 people and is spreading from village to village, government officials said. The World Health Organisation said the new outbreak was a previously unknown strain that provokes high fever before killing its victims without much blood haemorrhage. AFP PHOTO/stringer (Photo credit should read -/AFP/Getty Images)
ምስል Getty Images

ምእራብ ዩጋንዳ ውስጥ በፍጥነት በሚዛመተው ኤቦላ በተባለው በሽታ እንደተያዙ የሚጠረጠሩ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሄዱን መንግሥት አስታወቀ ። የበሽታውን ስርጭት የሚከታተሉ ተመራማሪዎች የኤቦላ ወረረሽኝ በአካባቢው መከሰቱን ካረጋገጡ ከጥቂት ቀናት በኋላ በበሽታው የተጠረጠሩ 6 ሰዎች ሆስፒታል መግባታቸው ተዘግቧል ። የዩጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ህዝቡ ራሱን ከበሽታው እንዲጠበቅ ጥሪ አስተላልፈዋል ። ገዳዩ ኤቦላ በወረረሽኝ መልክ የገባው 600 ሺህ ያህል ነዋሪ ባላት በምዕራብ ዩጋንዳዋ ኪባሊ ቀበሌ ውስጥ ነው ። ከዚሁ ቀበሌ የአንድ ቤተሰብ 9 አባላት አንዲት ነርስና የ 4 ወር ህፃን ልጅዋ በኤቦላ ህይወታቸው አልፏል ።  በዚሁ ቀበሌ በአንድ መንደር ተወስኖ የነበረው ኤቦላ

Relatives of Ebola patients wait outside the ward, wearing protective masks at Gulu hospital, northern Uganda, Thursday, Oct.19, 2000. Gulu hospital, a sprawling complex of concrete buildings, has been treating 45 people suspected of having the deadly ebola virus, that has so far killed 41 people and possibly infected 70 others. (AP Photo/Sayyid Azim)
የኤቦላ በሽተኞችምስል AP

አሁን ወደ ሌሎች መንደሮችም መዛመቱን የኪባሊ ቀበሌ የጤና ቢሮ ሃላፊውን ጠቅሶ አሶስየትድ ፕሬስ  ዘግቧል ። የኡጋንዳ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሃላፊዎችና የአለም የጤና ድርጅት ባለፈው ቅዳሜ እንዳሳወቁት በሐምሌ ወር ውስጥ 14 ኡጋንዳውያን በኤቦላ ቫይረስ ህይወታቸው አልፏል ። ኤቦላ ኡጋንዳ መግባቱ በተረጋገጠ በጥቂት ቀናት ውስጥ 6 በበሽታው ተይዘዋል ተብለው የተጠረጠሩ ህመምተኞች ሆስፒታል ገብተዋል ። ሰዎቹ የታመሙት በኤቦላ መሆኑ ከተረጋገጠ በበሽታው የተያዙትን ሰዎች ቁጥር ወደ 26 ከፍ ያደርገዋል ። የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ትናንት ለሃገራቸው ህዝብ ባስተላለፉት መልዕክት ህዝቡ አላስፈላጊ ከሆኑ የሰው ለሰው ንክኪዎች እንዲቆጠቡ ጠይቀዋል ።

« ኤቦላ ሰውነትን ከበሽታው አስተላላፊ ተውሃስ የሚከላከል መሳሪያ ባጠለቁ የህክምና ባለሞያዎች ነው ክትትል ሊደረግበት የሚገባው ። ከበሽታው ራሳችሁን እንድትጠበቁ ነው ጥሪ የማቀርበው ። እጅ አትጨባበጡ ፤ ኢቦላ በሚያሳያቸው ምልክቶች የሞተን ሰው  እናንተ አትቅበሩ ። ከዚያ ይልቅ ቀብሩ በጤና ባለሞያዎች እንዲከናወን አድርጉ ። ከሰዎች ጋር ከአካላዊ ግንኙነት ከማድረግ ተቆጠቡ  ። ምክንያቱም ይህ በሽታ በወሲብም ሊተላለፍ ይችላልና ። »

ARCHIV - Die Abbildung zeigt Ebola-Viren, die eng mit dem tödlichen Marburg-Virus verwandt sind (Archivfoto vom 11.5.1995). Eine Forscherin des Hamburger Tropeninstituts hat sich möglicherweise mit dem lebensbedrohlichen Ebola-Virus infiziert. Das wäre das erste Mal, dass sich ein Mensch in Deutschland mit Ebola angesteckt hat. Bei einem Unfall im Hochsicherheitslabor habe sich die Frau durch drei Paar Handschuhe hindurch mit einer Nadel verletzt. Foto: dpa dpa/lno +++(c) dpa - Bildfunk+++
የኤቦላ ቫይረስምስል picture-alliance/ dpa

ፕሬዝዳንቱ ከዚህ በተጨማሪም ህዝቡ የኤቦላ ጥርጣሬ ካለው ወዲያውኑ ለጤና ባለሞያዎች እንዲያሳውቅ አሳስበዋል ። የኤቦላ ወረርሽኝ ዩጋንዳ መግባቱን ለማረጋገጥ መርማሪዎች ወደ አንድ ወር የሚጠጋ ጊዜ ወስደዋል ። ሰኞ እንደተሰማው ኤቦላ በኪባሊ ቀበሌ ብቻ የተወሰነ መሆኑ ያጠራጥራል ። በመዲናይቱ ካምፓላ 2 ሰዎች የበሽታው ምልክት እንደታየባቸው ዲሊ ሞኒተር የተባለው ጋዜጣ ዘግቧል ። የኡጋንዳ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ግን ካምፓላ ውስጥ በኤቦላ የተያዘ ሰው የለም ሲል ዘገባውን አስተባብለዋል ። የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ሩክያ ናካማቴ ከኤቦላ በሽተኞች ጋር ንክኪ የነበራቸው የጤና ባለሞያዎችንም ሆነ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን ለይቶ ለማወቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል 

« እስካሁን ከሆስፒታሉ 34 የጤና ባለሞያዎች በበሽታው የተያዙ ሰዎችን አግኝተዋል ። እነዚህ ከበሽተኞች ጋር በመገኛኘት በክትትል የተገኙ ናቸው ። ከህብረተሰቡ ውስጥ የሚደረገው ክትትልም ጀምሯል ። እንደተባለው ክትትሉ ከቀጠለ በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር የነበሩ ሰዎች ቁጥር ይጨምራል»

ARCHIV - Mit einem Infektionsschutzanzug steht ein Rettungssanitäter der Feuerwehr Leipzig in einem Spezialfahrzeug in Leipzig (Archivfoto vom 20.02.2002). Der RITO-Wagen (Rettung, Intensivversorgung und Transport) kann bei Patienten mit den hochansteckenden Krankheiten wie Pocken, Lassa- und Ebola-Fieber, Milzbrand und Vogelgrippe-Virus eingesetzt werden. Bei einem 70 Jahre alten Afrikaner haben Ärzte in der Universitätsklinik Münster das seltene und gefährliche Lassa-Fieber festgestellt. Der aus Sierra Leone stammende Mann, der bis vor Kurzem noch als Chirurg in seinem Heimatland tätig war, sollte am Freitag Abend (21.07.2006) mit einem Isoliertransport in die auf solche Fälle spezialisierte Universitätsklinik Frankfurt/Main gebracht werden. Foto: Peter Endig (Zu dpa 4107) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ምስል picture-alliance/dpa

ኤቦላ ከአንዱ ወደ ሌላው በፍጥነት የሚተላለፍ ፣ ህይለኛ ትኩሳት የሚለቅ ፣ የአካል ውስጥ ደም መፍሰሰ የሚያስከትልና አጣድፎም የሚገድል በሽታ ነው ። ኃይለኛ ትኩሳት ራስ ምታት የሰውነት መገጣጠሚያና የጅማት ህመም እንዲሁም የጉሮሮ ቁስልና ድካም የበሽታው ምልክቶች ናቸው ። ሲበረታም ተቅማጥ ና ትውከት እንዲሁም የሆድ ህመም  ያስከትላል ።ሽፍታ ፣ የአይን መቅላት ፣ ስቅታ እንዲሁም የውጫዊና ውስጣዊ የሰውነት አካላት መድማትም በአንዳንድ በሽተኞች ላይ ይከሰታሉ ። በሽታው በቀጥታ ንክኪ ወይም በደም አለያም ከሰውነት በሚወጣ የትኛውም አይነት ፈሳሽ አማካይነት እንዲሁም በኤቦላ ቫይረሱ ከሞተ ሰው አስከሪን ጋር በሚደርግ ንክኪም ሊተላለፍ ይችላል ። የኤቦላ ወረረሽኝ በዩጋንዳ ሲከሰት እ.ጎ.አ ከ 2000 ወዲህ የአሁኑ ለ4 ተኛ ጊዜ መሆኑ ነው ። የመጀመሪያው የኤቦላ ወረርሽኝ በሰሜን ዩጋንዳ የ 224 ሰዎችን ህይወት አጥፍቷል ። በ 2007 ደግሞ 42 ሰዎች በዚሁ በሽታ ሞተዋል ። 

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ