የኤድስ ስርጭትና መድኃኒት ማከፋፈል በኢትዮጵያ19 ሐምሌ 2002ሰኞ፣ ሐምሌ 19 2002ኤች አይ ቪ በደማቸው ውስጥ ያለ ሰዎች በብዛት ከሚገኙባቸው ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ ናት ። ይሁንና በአሁኑ ሰዓት በሀገሪቱ የኤድስ በሽታን በሚያስከትለው ቫይረስ የሚያዙ አዋቂዎች ቁጥር ከቀደሙት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር መቀነሱን የመስኩ ባለሞያዎች ያስረዳሉ ።https://p.dw.com/p/OUymምስል picture-alliance/dpaማስታወቂያእንደ ባለሞያዎቹ አገላለፅ ከሰሀራ በታች ከሚገኙ ሌሎች የአፍሪቃ አገራት ጋር ሲወዳደርም በኢትዮጵያ አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር እየወረደ መጥቷል ። የፀረ ኤች አይ ቪ መድኃኒት ስርጭትም ከቀድሞው በተሻለ ደረጃ ላይ ይገኛል ። ሆኖም ካቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ሰዎች እንደሚሉት የተጓዳኝ በሽታዎች ህክምና አለመሟላት አንዱ ዓብይ ችግራቸው ነው ። ሂሩት መለሰ ሸዋዮ ለገሰ