1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኦጋዴን ችግርና የቀድሞዉ የአካባቢዉ ወጣቶች መሪ

ረቡዕ፣ ጥር 8 2005

እስከተሰደደበት ድረስ የኖረበትን፥የኦጋዴንን ችግር-ለማቃለል ብልሐቱ ሁለት ነዉ-ባይ ነዉ-አብዱላሒ።በወጣትነት እድሜዉ «በቂ» የሚባል ሥልጣን፥ሥራዉን ምናልባትም ጥሩ ገቢ፥ ሐገር ኑሮዉን ትቶ ለመሰደዱ ምክንያት-የሚለዉ ብዙ ነዉ።ዋናዉ ግን በኦጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰዉ በደልና የሹማምንታቱ አሰልቺ «ዉሸት» ናቸዉ ይላል።

https://p.dw.com/p/17LDO
An ethnic Somali woman herds goats outside the town of Gode in the Ogaden region of eastern Ethiopia in January 2006. Journalists have been barred from the remote, isolated Ogaden region for much of 2007 as the Ethiopian military carries out a shadowy military campaign against a separatist rebel group known as the Ogaden National Liberation Front, or ONLF. Refugees and human rights groups charge the Ethiopian military with terrorizing and killing and civilians and forcibly recruiting villagers to fight the rebels, charges that the government denies. Foto: Shashank Bengali/MCT /Landov +++(c) dpa - Report+++
የኦጋዴንምስል picture alliance/dpa

የሶማሊያ መሥተዳድር ልዩ ፖሊስ ሠላማዊዉን ሕዝብ እንደሚበድል፥ ሠብአዊ መብት እንደሚጥስ እና እንደሚዘርፍ የቀድሞዉ የሶማሌ መስተዳድር የወጣቶች ፌደሬሽን ሊቀመንበር እና የመስተዳሩ አምደ-መረብ (ኢንተርኔት) ሐላፊ አስታወቀ።በቅርቡ ከሐገር የወጣዉ ወጣት አብዱላሒ ሁሴን እንደሚለዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ በአሸባሪነት ወንጀል ተፈርዶባቸዉ በይቅርታ በተለቀቁት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች ላይ ቀርቦ የነበረዉን የቪዲዮ መረጃም በመስተዳድሩ ልዩ ፖሊስ የተዘጋጀ «የሐሠት ፊልም» ብሎታልም።የኢትዮጵያ መንግሥት ኦጋዴን ዉስጥ ሠላም ለማስፈን ከፈለገ ከኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጪ ግንባር (ኦብነግ) ጋር እንዲደራደርም ወጣቱ መክሯል።

የብሪታንያ መንግሥት በቅርቡ ሶማሌ መስተዳድር ለሠፈረዉ ልዩ ፖሊስ ማሠለጠኛ እስከ አስራ-አምስት ሚሊዮን ፓዉንድ የሚደርስ እርዳታ ለመስጠት መዘጋጀቱ የመብት ተሟጋቾችን ተቀዉሞ ቀስቅሷል።አምንስቲ ኢንተርናሽናል እና ሑዩማን ራይትስ ዋችን የመሳሰሉ ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች እንደሚሉት የብሪታንያ መንግሥት ይረዳዋል የተባለዉ ልዩ ፖሊስ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ረገጣ የሚፈፅም ሐይል ነዉ።

የብሪታንያ መንግሥት ርዳታዉ ለልማት እንጂ መብት ይረግጣል ለተባለዉ ሐይል አይዉልም ባይ ነዉ።አብዱላሒ ሁሴይን ግን የመብት ተሟጋች ድርጅቶቹን ሐሳብ ነዉ-የሚጋራዉ።


የሶማሌ መስተዳድርን በመወለድ፥ ማደግ እና በመኖር ጠንቅቆ ያዉቀዋል።የአካባቢዉን ፖለቲካዊ ዉጥንቅጥ የሚያዉቅበት መንገድ ደግሞ ብዙ ነዉ።የሶማሌ መስተዳድር የወጣቶች ፌደሬሽን ሊቀመንበር፥ የኢትዮጵያ የፌደራል ወጣቶች ማሕበር ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልም ነበር። በመስተዳድሩ ፕሬዝዳት ቢሮ የሚዘጋጀዉ «ሐካራ ኒዊስ» የተሰኘዉ አምደ-መረብ ሐላፊም ነበር።


እስከተሰደደበት ድረስ የኖረበትን፥የኦጋዴንን ችግር-ለማቃለል ብልሐቱ ሁለት ነዉ-ባይ ነዉ-አብዱላሒ።በወጣትነት እድሜዉ «በቂ» የሚባል ሥልጣን፥ሥራዉን ምናልባትም ጥሩ ገቢ፥ ሐገር ኑሮዉን ትቶ ለመሰደዱ ምክንያት-የሚለዉ ብዙ ነዉ።ዋናዉ ግን በኦጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰዉ በደልና የሹማምንታቱ አሰልቺ «ዉሸት» ናቸዉ ይላል።

ከሐገር ሲወጣ ከቋጠራቸዉ ሰነዶች መሐል ኢትዮጵያ ዉስጥ በአሸባሪነት ወንጀል እያንዳዳቸዉ አስራ-አንድ ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዉ በነበሩት ሁለት የሲዊድን ጋዜጠኞች ላይ በመረጃነት ቀርቦ የነበረዉ ቪዲዮ አንዱ ነዉ።


ሐምሌ-ሁለት ሺሕ ሰወስት ኦጋዴን ዉስጥ የተያዙት ዮሐን ፔርሰንና ማርቲን ሺብዬ ወደ ኢትዮጵያ የገቡት በሕገወጥ መንገድ መሆኑ አላነጋገረም።እነሱም አልካዱምም።የኢትዮጵያ መንግሥት አሸባሪ ከሚለዉ ከኦብነግ ታጣቂዎች ጋር ማበራቸዉን፥ ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር መታኮሳቸዉን የሚያሳዉ ፊልም ግን አብዱላሒ እንደሚለዉ የሐሰት ነዉ።


ሁለቱ ጋዜጠኞች የ«ሐሰት» የተባለዉን ቪዲዮ በሐራቸዉ መገናኛ ዘዴዎች አሰራጭተዉታል።

ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ













epa03040270 (FILE) A handout picture taken in 2010 and provided by Kontinent Agency on 18 October 2011 shows Swedish photojournalist Johan Persson on assignment at an undisclosed location. Reports state that a court in Ethiopia on 21 December 2011 found Persson and his colleague and journalist Martin Schibbye guilty of supporting terrorism after the pair illegally entered the country from Somalia with the rebel Ogaden National Liberation Front (ONLF). The pair now face up to 15 years in prison. Swedish Prime Minister Frederick Reinfeldt said in a statement that they should be freed as soon as possible as they have been in the country on a journalistic mission. Their next court appearance is scheduled for 27 December 2011 when sentencing could occur. EPA/KONTINGENT AGENCY SWEDEN OUT HANDOUT EDITORIAL USE ONLY/NO SALES +++(c) dpa - Bildfunk+++
ጋዜጠኛ-ፔርሰንምስል picture-alliance/dpa
epa03040271 (FILE) A handout picture taken in 2009 and provided by Kontinent Agency on 18 October 2011 shows Swedish journalist Martin Schibbye on assignment in the Philippines. Reports state that a court in Ethiopia on 21 December 2011 found Schibbye and his colleague and photojournalist Johan Persson guilty of supporting terrorism after the pair illegally entered the country from Somalia with the rebel Ogaden National Liberation Front (ONLF). The pair now face up to 15 years in prison. Swedish Prime Minister Frederick Reinfeldt said in a statement that they should be freed as soon as possible as they have been in the country on a journalistic mission. Their next court appearance is scheduled for 27 December 2011 when sentencing could occur. EPA/KONTINGENT AGENCY / HANDOUT SWEDEN OUT HANDOUT EDITORIAL USE ONLY/NO SALES +++(c) dpa - Bildfunk+++
ጋዜጠኛ-ሺብዬምስል picture-alliance/dpa