1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኩላሊት ንቅለ ተከላ

ሰኞ፣ መስከረም 22 2010

የማዕከሉ ሃላፊዎች በዚህ ሳምንት ማዕከሉን ለጎበኙ ጋዜጠኖች እንደተናገሩት ህክምናውን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ለማካሄድ በኩላሊት ንቅለ-ተከላ የሚሰማሩ ሐኪሞች በሀገር ውስጥ እየሰለጠኑ ነው።

https://p.dw.com/p/2kzsv
Äthiopien Addis Abeba Nieren-Transplantation
ምስል DW/Getachew Tedla

የኩላሊት ነቀላ እና ተከላ

በአዲስ አበባው የጳውሎስ ሆስፒታል የሚገኘው የኩላሊት ንቅለ ተከላ ማዕከል ህክምናውን በቅርቡ ያለምንም የውጭ እርዳታ ማካሄድ የሚችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀ። የማዕከሉ ሃላፊዎች በዚህ ሳምንት ማዕከሉን ለጎበኙ ጋዜጠኖች እንደተናገሩት ህክምናውን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን ለማካሄድ በኩላሊት ንቅለ-ተከላ የሚሰማሩ ሐኪሞች በሀገር ውስጥ እየሰለጠኑ ነው። ከረዥም ጊዜ ጥረት በኋላ በኢትዮጵያ መሰጠት የጀመረው ይህ ህክምና በዓይነቱ ልዩ መሆኑንንም ሃላፊዎቹ ተናግረዋል። ማዕከሉን የጎበኘው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ቀጣዩን ዘገባ አዘጋጅቷል። 
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ