1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኮሪያ ልሳነ ምድር ዉጥረት እና የአዉሮጳ ሕብረት

ዓርብ፣ ጳጉሜን 3 2009

የሕብረቱ ባለሥልጣናት እንደሚሉት የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት ሰሜን ኮሪያ በተጨማሪ ማዕቀብ መቅጣት አለበት።የዚያኑ ያክል ማዕቀቡ  የፒዮንግዮንግ ባለሥልጣናትን ወደ ድርድር እንዲመለሱ ከማስገደድ ያለፈ ዓላማ  ሊኖር አይገባም ባይ ናቸዉ

https://p.dw.com/p/2jbul
Belgien EU-Flaggen auf Halbmast in Brüssel

European flags fly at half-mast to pay tribute to the victims of the terrorist attack in the Christmas Market in Berlin, Germany)
ምስል EU/J. Jacquemart

(Q&A) Nordkoria-EU - MP3-Stereo

ሰሜን ኮሪያ ከዩናይትድ ስቴትስ፤ ከደቡብ ኮሪያና ከጃፓን ጋር የገጠመችዉን የዉጊያ ዛቻ እና ፍጥጫ ለማስቆም ቅጣት ከድርድር የቀየጠ መፍትሔ እንዲፈለገ የአዉሮጳ ሕብረት ጠየቀ።የሕብረቱ ባለሥልጣናት እንደሚሉት የፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት ሰሜን ኮሪያ በተጨማሪ ማዕቀብ መቅጣት አለበት።የዚያኑ ያክል ማዕቀቡ  የፒዮንግዮንግ ባለሥልጣናትን ወደ ድርድር እንዲመለሱ ከማስገደድ ያለፈ ዓላማ  ሊኖር አይገባም ባይ ናቸዉ።በኮሪያ ልሳነ ምድር የሚደረገዉ የዉጊያ ዝግጅት፤ የወታደር እና የጦር መሳሪያ ክምችት እንዲቆምም ሕብረቱ ጠይቋል።የብራስልሱ ወኪላችን ገበያዉ ንጉሴን በስልክ አነጋግሬዉ ነበር።

ገበያዉ ንጉሴ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ