የውጭ አገር የስራ ስምሬት አዋጅና ኢትዮጵያውን
ረቡዕ፣ ግንቦት 10 2008ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሥራ ወደ ውጭ ለሚሄዱ ዜጎች ይጠቅማል የተባለ አዋጅ ካፀደቀ አራት ወር ሆኗል። ይኽው የኢትዮጵያ የውጭ አገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ፣ በተለይ በመካከለኛው ምሥራቅ በቤት ሠራተኝነት የተሰማሩ ዜጎች ከዚህ ቀደም ይደርስባቸው የነበረውን እንግልትና ስቃይ ያስቀራል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል። ሕጉ ዜጎችን ወደ መካከለኛው ምሥራቅ ሃገራት በመላክ የተሰማሩ ሕገ ወጥ ደላሎችን ለመቆጣጠር እንደሚያስችልም ተነግሯል። ለመሆኑ ይህ ሕግ ሠራተኛ በሚሄድባቸው ሃገራት ዘንድ ተቀባይነቱ እስከምን ድረስ ነው? ሕጉ ከወጣ ወዲህስ ምን ለውጦች አሉ? የሪያድ ነዋሪ የሆነውን ስለሺ ሽብሩን በስልክ አነጋግረነዋል። በቅድሚያ ስለ ኢትዮጵያ የውጭ አገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ምንነትና ከቀደመው ተመሳሳይ ሕግ በምን እንደሚለይ በማስረዳት ይጀምራል።
ስለሺ ሽብሩ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ