1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የቃል አቀባይ አቶ መለስ መግለጫ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 22 2010

አቶ መለስ ዓለም ዛሬ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሕገ ወጥ መንገድ ዛምብያ ገብተዋል የተባሉት ስደተኞች ወደ ሀገራቸው በሚመለሱበት ጉዳይ ላይ ከዛምብያ መንግሥት ጋር ድርድር እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።

https://p.dw.com/p/2ms4q
Äthiopien Meles Alem Sprecher Außenministerium
ምስል DW/G. Tedla

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ

ዛምቢያ የሚገኙ የታሰሩ 118 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የመሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አቶ መለስ ዓለም ዛሬ ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሕገ ወጥ መንገድ ዛምብያ ገብተዋል የተባሉት ስደተኞች ወደ ሀገራቸው በሚመለሱበት ጉዳይ ላይ ከዛምብያ መንግሥት ጋር ድርድር እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል። ቃል አቀባዩ ኤች አር 128 በሚል ስያሜ ተዘጋጅቶ ለአሜሪካን ምክር ቤት ስለቀረበው እና ኢትዮጵያን ስለተመለከተው ረቂቅ ሕግ ለቀረበላቸው ጥያቄም መልስ ሰጥተዋል። ጋዜጣዊ መግለጫውን የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ጌታቸው ተድላ ኅይለ ጊዮርጊስ ተከታትሏል።

ጌታቸው ተድላ ኅይለ ጊዮርጊስ

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሰ