1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዐባይ ተፋሰስ አገሮች ትብብር ወይስ ድብቅ ፍጥጫ፣

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 4 2005

ነጭ ዓባይና ጥቁር ዓባይ የሚመነጬባቸውና የሚያጠጧቸው አገሮች፤ ውሃውን በአግባቡ ፍትኀዊ በሆነ መልኩ በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ትብብር ይኖር ዘንድ ለብዙ ዓመታት ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው አይካድም። ብዙኀኑ አባላት ይህን የትብብር ፈለግ ሲመርጡ

https://p.dw.com/p/1724r
ምስል CC/Lourdes Cardenal

፤ ሱዳንና ግብፅ፣ በተለይ አሁን የህዝቧ ቁጥር 80 ሚሊዮን መድረሱ የሚነግርላት ግብፅ፤ ከትብብር ይልቅ ወታደራዊ ጡንቻን እንደ አማራጭ ይዛ ከማሰላሰል አለመቦዘኗን አንዳንድ መገናኛ ብዙኀን ይጠቁማሉ። የተፋሰሱን ሃገራት የትብብር አቋም የሚመረምሩ ምን ይላሉ?

Blauer Nil Wasserfall Äthiopien
ምስል DW/Azeb Tadesse Hahn

ውሃ ህይወት ነው። በተለይ ምድረ በዳ የሆነ አገር ላላቸው ሰዎች፤ የውሃ ሀብት እጅግ ላቅ ያለ ትርጉም ነው የሚሰጠው።ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ግብፅ ናት። በዐባይ ወንዝ ላይ ህልውናዋ የተመሠረተው ግብፅ፤ ለውሃው ከመሠሠቷ የተነሣ፣ ውሃው የሚመንጭባቸው አገሮች በተፈጥሮ ሃብታቸው ያላቸውን የመጠቀም መብት በጭፍኑ ማወቅ እንደማትሻ ተስተውሏል።

ከሞላ ጎደል ሁሉም የተፋሰሱ ሃገራት ውሃውን ፍትኃዊ በሆነ መልኩ ለራሳቸውና በጋራም መጠቀም አግባብነት አለው ብለው ቢያምኑም፤ በተለይ ግብፅና ሱዳን የሚፈለገውን ያህል ሲተባበሩ አይታዩም። አንዳንዴም በምሥጢር ፤ በተለይ ግብፅ የኃይል እርምጃ የመውሰድ፣ ማለት በጦር ኃይል የመጠቀም ዓላማ ያላት መሆኑን አንዳንድ የመገናኛ ብዙሃን አውታሮች መጠቆማቸውን ልብ ይሏል።

Flash-Galerie Brückenneubau in Khartoum
ምስል Picture-Alliance/dpa

የዐባይ ተፋሰስ አገሮችየወደፊት አካሄድ በትብብር ወይስ በፍጥጫ የተመረኮዘ ነው?ባለፉት 38,39 ዓመታት ገደማበውሃና አካባቢ ጥበቃ መሥክ ሥራ ላይ ፤ በመንግሥት መ/ቤትም በግልም የሠሩት፤ ካርቱም ውስጥ፤ ለ 6 ዓመታት ያህል በናይል ተፋሰስ አገሮች፣ የትብብር መድረክ ቢሮ የሠሩትና አሁን፤ በግል በማማከር ተግባር ላይ የተሠማሩት ኢንጂኔር ጌዴዎን አስፋው ፣ እንዲህ ይላሉ።

Merowe Staudamm, Sudan
ምስል Lubumbashi

6 የዐባይ ተፋሰስ አገሮች፤ የትብብሩን ውል የፈረሙ ሲሆን፣ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፓብሊክም ይህን ታደረጋለች ተብላ በመጠበቅ ላይ ናት። ደቡብ ሱዳንም የብዙኀኑን ፈለግ የመከተል ፍላጎት እንዳላት ነው የሚነገረው። ግብፅና ሱዳን፤ ኢንጂኔር ጌዴዎን ጌታሁን እንደሚሉት፤ የሁኔታዎች ለውጥ መኖሩን በመገንዘብ፤ ከመተባበር ሌላ ተቃራኒውን መንገድ የመከተሉ ሂደት እንደማያዋጣ ሳይገነዘቡ አልቀሩም።

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሰ