1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም ሙቀት መጨመርና ሰበቡ

ዓርብ፣ መስከረም 17 2006

ባለፉት 60 ዓመታት እየጨመረ ለመጣው የዓለማችን ሙቀት አብዩ ምክንያት ሰው ሰራሽ መሆኑን ዛሬ ይፋ የሆነ አንድ ጥናት አስታወቀ ።

https://p.dw.com/p/19pdU
ምስል picture-alliance/dpa

የተባበሩት መንግሥታት የዓየር ንብረት ለውጥ አጥኚዎች ቡድን ዛሬ እንዳስታወቀው የዛሬ 6 ዓመት ባቀረበው ዘገባ ለዓለማችን ሙቀት መጨመር የሰው ልጅ ድርሻ 90 በመቶ ነው ሲል የዘገበውን አሁን ወደ 95 በመቶ ከፍ አድርጎታል ። ችግሩን ለመከላከልም መንግስታት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስዱና እጎአ እስከ 2015 አንድ የጋራ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ቡድኑ ጠይቋል ። ዛሬ ስቶክሆልም ስዊድን ውስጥ ይፋ የተደረገው ይኽው ዘገባ ባለ 2 ሺህ ገፅ ሲሆን ለፖሊሲ አውጭዎች የተዘጋጀ ተጨማሪ 36 ገፅ ማጠቃለያም አለው ። ዘገባው የተቀመረው በ 257 ሳይንቲስቶች ነው ። ስለዚሁ ዘገባ ስቶክሆልም ስዊድን የሚገኘውን ወኪላችንን ቴዎድሮስ ምህረቱን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ ጠይቄው ነበር ።

ቴዎድሮስ ምህረቱ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ