1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዓለም ባንክ አዲስ ፕሬዚደንት መምረጡ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 9 2004

አሜሪካዊው ጂም ጆንግ ኪም አዲሱ የዓለም ባንክ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ። እንደሚታወቀው ለባንኩ ፕሬዚደንትነት ሥልጣን ከኪም ጎን የናይጀሪያ የገንዘብ ሚንስትር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላም ተወዳድረው ነበር።

https://p.dw.com/p/14fPt
ARCHIV - Der Präsident des Dartmouth College, Jim Yong Kim, lächelt am 23.03.2012 im Garten des Weißen Hauses in Washington, USA. US-Präsident Obama will Jim Yong Kim als neuen Weltbankchef - und nach alter Tradition ist sein Wunsch Befehl. Doch erstmals gibt es heftigen Widerstand gegen den US-Kandidaten. Foto: EPA/ANDREW HARRER/POOL (Zu dpa «Tradition oder Revolution? Weltbank bestimmt neuen Präsidenten» vom 15.04.2012) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ዶክተር ጂም ዮንግ ኪምምስል picture-alliance/dpa

የዕጩነቱን ጥያቄ በተመለከተ ብዙ አሻሚ ሀሳቦች ቀርበው እንደነበር አይዘነጋም። በተለይ ናይጀሪያዊትዋ የገንዘብ ሚንስትር በአሜሪካዊው ተፎካካሪያቸው አንጻር የምጣኔ ሀብት ምሁር በመሆናቸው፡ በአፍሪቃዊነታቸውና በሴትነታቸው የተነሳ በዓለም ትልቁን የልማትና ብድር ሰጪ ድርጅት የሆነውን የዓለም ባንክ እንዲመሩ የፈለጉ ጥቂቶች አልነበሩም። ያም ሆኖ ግን ዩኤስ አሜሪካ የራሷን ዕጩ ማስመረጡ እንደተጠበቀው ተሳክቶላታል። እርግጥ፣  የናይጀርያዋ የገንዘብ ሚንስትር እና  የቀድሞዋ የዓለም ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንትንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላ ፕሬዝደንት ሆነዉ ለተመረጡት ተፎካካሪያቸዉ ለጂም ዮንግ ኪም የእንኳን ደስ ያልዎት መልእክት ቢያስተላልፉም፣ አቡጃ ላይ ባደረጉት ንግግራቸው የምርጫዉ ሂደት ግልጽ መሆንና  ችሎታን ያመዛዘነ መሆን ነበረበት ሲሉ ቅሬታቸዉን አሰምተዋል። እና በአዲሱ የዓለም ባንክ ፕሬዚደንት ምርጫ ሂደት ዩኤስ አሜሪካ የዓለም ባንክ አባል ሀገሮችን ድጋፍ ለማግኘት የተጠቀመችበት ዘዴ ወይም በአባላቱ ላይ ያሳረፈችባቸው ተፅዕኖ ነበር ወይ? ቀደም ሲል በምርጫው ሂደት ላይ በስልክ ያነጋገርኩትን የዋሽንግተኑን ወኪላችን አበበ ፈለቀን በመጀመሪያ ጠይቄው ነበር።

Ngozi Okonjo-Iweala, coordinating minister for economy and finance of Nigeria, speaks during a plenary session at the 42nd annual meeting of the World Economic Forum, WEF, in Davos, Switzerland, Thursday, Jan. 26, 2012. The overarching theme of the meeting, which will take place from Jan. 25 to 29, is "The Great Transformation: Shaping New Models". (Foto:Keystone, Jean-Christophe Bott/AP/dapd)
የናይጀሪያ የገንዘብ ሚንስትር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዌላምስል dapd

አበበ ፈለቀ

አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ