1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩናይትድ ስቴትስ መርህና ኢትዮጵያ

እሑድ፣ ሚያዝያ 25 2007

ከሳምንታት በፊት በዩናይትድ ስቴትስ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በምክትልነት የተሰየሙት ዌንዲ ሻርማን ኢትዮጵያን ለአጭር ቀናት ጎብኝተዉ ነበር።

https://p.dw.com/p/1FIuK
USA-Afrika-Gipfel in Washington 05.08.2014
ምስል Reuters

አሜሪካዊቱ ፖለቲከኛ ዌንዲ ሻርማን በዚህ ወቅት የሀገሪቱን አስተዳደርና የምርጫ ይዞታ አስመልክተዉ የሰነዘሩት አስተያየት በራሳቸዉ ላይ ትችት ከማስከተሉ ባሻገር የሚሠሩበት መሥሪያ ቤት የዩናይትድ ስቴትስ የዉጭ ጉዳይ ጉዳይ ሚኒስቴር በየዓመቱ የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታ አስመልክቶ ከሚያወጣዉ ዘገባ የሚጣረስ መሆኑ ግርምትና ጥያቄዎችን አስከትሏል። ኢትዮጵያዉያንን ጨምሮም ዓለም ዓቀፍ የመብት ተሟጋቾችና ገለልተኛ አጥኚዎች ትችታት ተቃዉሟቸዉን በይፋ አሰምተዋል። ትችትና ተቃዉሞዉም ለመሆኑ የዩናይትድ ስቴትስ የዉጭ ጉዳይ ፖሊሲ ወይም መርህ ምንድነዉ? ተለዉጧልስ ወይ የሚል ጥያቄን ያዘለ ነዉ። ዶይቼ ቬለም የዚህ ሳምንት የእንወያይ ርዕሱ አድርጎታል።

ሸዋዬ ለገሠ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ