1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩጋንዳዉ አማፂ ቡድን ግፍ

ዓርብ፣ ኅዳር 12 2007

።«ልጁ ወላጆቹን እንዲገድል ይታዘዛል።ልጁ ትዕዛዙን ሲፈፅም ወድሞቹ፤የአክስት አጎት ልጁቹ እና ሌሎች ዘመዶቹም እንዲያ ይገደዳሉ።ከዚያ በሕዋላ ገዳዩን ወላጆቹን ወይም ዘመዶቻችንን የገደለ እያሉ እረፍት ያሳጡታል።እሱም እነሱም የተሠራዉን አይረሱም

https://p.dw.com/p/1DrLb
ምስል picture-alliance/dpa/Price

የፈጣሪ መከላከያ ጦር (LRA-በእንግሊዝኛ ምሕጻሩ) የሚያግታቸዉ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።የድርጅቱ ዘገባ እንዳመለከተዉ ዩጋንዳን በአሥርቱ የመፅሐፍ ቅዱስ ትዕዛዛት መሠረት ለመግዛት ያለመዉ ጨካኝ ቡድን ባለፉት አሥራ-አንድ ወራት ብቻ 432 የማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ ዜጎችን አፍኖ ወስዷል።በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት በጦር ወንጀለኝነት ተከሶ የሚታደነዉ ጆሴፍ ኮኒ የሚመራዉ ቡድን ከየሥፍራዉ እያፈነ የሚወስዳቸዉ አብዛኞቹ ታዳጊ ወጣቶች ናቸዉ። ክሎታ ዋንጆሒ የዘገበችዉን ነጋሽ መሐመድ አጠናቅሮታል።

የአፍሪቃ ሕብረት ጦር እንደሚለዉ ጆሴፍ ኮኒን ለመያዝ ጦሩ ከዘመተ ጀምሮ አሸባሪዉ ቡድን ባብዛኛዉ ዩጋንዳ፤ አልፎ አልፎ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፕብሊክና ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፕክሊክ ዉስጥ-ሰዎችን አካላታቸዉን እየቆራረጠ፤ በየጎጆቸዉ እሳት እየለቀቀ፤ ሲያሰኘዉ በጥይት እየረሸነ-መግደል ማሰቃየቱ ቀንሷል።

የሕብረቱ ጦር የመረጃ አስተባባሪ ሻምበል ሉዊስ ቻርልስ ፤ዩጋንዳ መራሹ የአፍሪቃ ሕብረት ጦር እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር በ2010 ቡድኑን ማጥቃት ከጀመረ ወዲሕ፤ ቡድኑ አደጋ የማድረስ አቅሙም ተዳክሟ።«ከ2010 ወዲሕ የዉጊያ ሥልታቸዉን ለዉጠዋል።እንደ መደበኛ ቡድን ሆነዋል።አካላት መቆራረጣቸዉን አቁመዋል።የሚገድሉትም ሕልዉናቸዉን ለማስጠበቅ ሲሉ ነዉ።»

Uganda LRA Opfer
ምስል picture-alliance/dpa

የአፍሪቃ ሕብረት ጨካኙን ቡድኑን የሚወጋ አምስት ሺሕ ጦር ለማዝመት ወስኖ ነበር። ዩጋንዳ ሁለት ሺሕዉን ለማዋጣት ቃል ስትገባ፤ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ፤ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ፤ እና ደቡብ ሱዳን እያንዳዳቸዉ አንዳድ ሺሕ ጦር ያዋጣሉ ነበር-ቃል ተስፋዉ።

አልሆነም።ሁሉም በየራሳቸዉ ችግር ሲወጠሩ ቡድኑን ለመዉጋት የዘመተዉ 1500-የዩጋንዳ፤ 500 የተቀሩት ሐገራት ጦር ብቻ ነዉ።2000 በድምሩi።ሻምበል ቻርልስ እንደሚሉት የጦሩ ቁጥር፤የዘመቻዉ ዉጤትም የተፈለገዉን ያሕል ባይሆንም ዘመቻዉ የቡድኑን አቅም በጅጉ አዳክሞታል።«የቡድኑ አባላት ሰዎችን የሚያግቱት ላጭር ጊዜ ነዉ።ካንድ ሁለት ቀናት በኋላ ይለቋቸዋል።ታጋቾቹን የሚጠቀሙባቸዉም ዕቃ እንዲሸከሙ ነዉ።መንደሮችን አያቃጥሉም።የሚዘርፉትም እራሳቸዉን ለማቆየት ያሕል ብቻ ነዉ።»

የአሸባሪዉ ቡድን ጨካኝ መሪ ግን እስካሁን ያለበት አይታወቅም።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጥናትም በተለይ እገታን በመለከተ ከሻምበሉ መግለጫ ጋር ይቃረናል።ከጥር እስከ እስካሁን በተቆጠሩት አሥራ-አንድ ወራት ዉስጥ ብቻ፤ካንዲት ማዕከላዊ አፍሪቃ ብቻ ከ430 በላይ ወጣቶችን አግቷል።አምና እና ዘንድሮ የታገቱት ወጣቶች ቁጥር ሐቻምና ከታገቱት በጅጉ ጨምሯል።

ታጋቹ ወንድ ከሆነ-በተዋጊነት፤በተሸካሚነት፤በተዋጊ-አዋጊዎች ተላላኪነት ያገለግል።ሴቶችና ልጃገረዶች በአብዛኛዉ የአዋጊዎች የጭን ገረድ ናቸዉ።የወሲብ ባሪያ።« እግሬን ግጥም አድርገዉ በገመድ አሠሩት። እና ወሰዱኝ።ጫካ ከወሰዱኝ በኋላ ሁሉንም ከባድ ነገር ያሰሩናል።የአማፂያኑን ዕቃ አሸክመዉ እንድናጓጉዝ ያደርጉናል።ያንን ጌዜ ሳስበዉ ልቤ ይደማል።»ትላለች ኔሲፒዮ ታሻና።ስትታገት አሥራ-ስድት ዓመቷ ነበር።አምልጣ-ደቡብ ሱዳንዋ ከተማ ያመቢዮ የገባችዉ-ሁለት ራስዋን ነበር።

Uganda Soldaten Suche nach Joseph Kony Archivbild
ምስል picture alliance/Yannick Tylle

በደቡብ ሱዳንዋ የምዕራብ ኢኳቴሪያል ግዛት ዋና ከተማ ያምቢዮ ከአሸባሪዉ ቡድን ያመለጡ፤ ወይም የአፍሪቃ ሕብረት ጦር ያስጣላቸዉ ታጋቾች የሚሰፍሩበት ጌዚያዊ ማዕከል አለ።ብዙዎቹ ሴቶች ወደ እዚሕ ሠፈር የሚመጡት ከአማፂያኑ ከወለዷቸዉ ልጆች ጋር ነዉ።

የመጠለያዉ ማዕከል ሐላፊ ጀስቲን ኢቤሬ እንደሚሉት አማፂዉ ቡድን በወንዶቹ ታጋቾች ላይ የሚፈፅመዉ በደልም ዘግናኝ ነዉ። አካላዊም-መንፈሳዊም።«ልጁ ወላጆቹን እንዲገድል ይታዘዛል።ልጁ ትዕዛዙን ሲፈፅም ወድሞቹ፤የአክስት አጎት ልጁቹ እና ሌሎች ዘመዶቹም እንዲያ ይገደዳሉ።ከዚያ በሕዋላ ገዳዩን ወላጆቹን ወይም ዘመዶቻችንን የገደለ እያሉ እረፍት ያሳጡታል።እሱም እነሱም የተሠራዉን አይረሱም።ሥለዚሕ ገዳዩ ከገዛ ዘመዶቹ ይገለላል።ዘምድናዉም ይሰበራል።»

የቡድኑ አባላት ቁጥር መቀነሱ ይነገራል።ግን ገና ክፉን-ደጉን ሳይለዩ በወላጅ-ዘመዶቻቸዉ ላይ ዘግናኝ ወንጀል ፈፅመዉ-ቡድኑን የተቀየጡት ወጣቶች የፈፀሙትንና የተፈፀመባቸዉን ግፍ ላለመቀጠላቸዉ ምንም ዋስትና የለም።

ነጋሽ መሐመድ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ