የደቡብ ሱዳን ሕዝበ ዉሳኔ: አዉሮጳ ሕብረትና ኢጋድ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 14 2003ማስታወቂያ
የደቡብ ሱዳን ሕዝበ ዉሳኔና አዉሮጳ ሕብረት
የአዉሮጳ ሕብረት የሱዳን መንግሥትና የቀድሞዉ የደቡብ ሱዳን ነፃ አዉጪ ንቅናቄ ከአምስት አመት በፊት የተፈራራሙትን ሥምምነት ገቢር ለማድረግ ከእንግዲሕ የሚያደርጉትን ድርድር ለማገዝ ዝግጁነኝ አለ።የሕብረቱ የሚንስትሮች ምክር ቤት ትናንት በጉዳዩ ላይ ከተነጋገረ በሕዋላ ባወጣዉ መግለጫዉ በመጪዉ ጥር ደቡብ ሱዳን ዉስጥ የሚደረገዉን ሕዝበ ዉሳኔ የሚታዘብ ቡድን እንደሚልክም አስታዉቋል።መገለጫዉ መሠት ሕብረቱ የደቡብ ሱዳንንም ሆነ የዳርፉርን ችግር ለማስወገድ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ጉዳዩ ከሚመለከታቸዉ ወገኖች ጋር ተባብሮ ይሠራል።
---------------------
የአውሮፓ ኅብረት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች ፣በብራሰልስ ውስጥ ባደረጉት ጉባዔ፣ ለደቡብ ሱዳን ህዝበ- ውሳኔ መሳካት የበኩላቸውን ድርሻ ለማበርከት መዘጋጀታቸውን የገለጡ ሲሆን፣ የኢጋድ አባል መንግሥታት መሪዎችም፣ አንዳንድ ሳንኮች ይወገዱ ዘንድ ከሱዳን መሪዎች ዖማር አል በሺርና ሳልቫ ኪር ጋር መክረዋል።
ገበያዉ ንጉሴ
ታደሰ እንግዳዉ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ