1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደቡብ ሱዳን ግጭት ሰለባ የሆኑ ኢትዮጵያውያን

ሰኞ፣ ታኅሣሥ 21 2006

ንብረታቸውን ተዘርፈው ባዶ እጃቸውን ነው ወደ ጁባ የመጡት ። እኚሁ ነዋሪ ዝርፊያው በአማፅያኑም በመንግሥት ወታደሮችም እንደተካሄደ ነው የሚናገሩት ።

https://p.dw.com/p/1AjFF
ምስል picture-alliance/dpa

የደቡብ ሱዳኑ ግጭት መዘዝ እዚያ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ተርፎ ዜጎች ለልዩ ልዩ ጥቃቶች መጋለጣቸውን መናገር ከጀመሩ ቆይተዋል ። በአሁኑ ጊዜ እዚያ ከሚገኙት ኢትዮጵያውያን የተወሰኑት በአውሮፕላንና በጀልባ ወደ ሃገራቸው እየተመለሱ ነው ። በስልክ ያነጋገርናቸው አንድ የጁባ ነዋሪ እንዳሉት በተለይ ግጭቱ ያየለባቸው አካባቢዎች የነበሩት ኢትዮጵያውን ሃብት ንብረታቸውን ተዘርፈው ባዶ እጃቸውን ነው ወደ ጁባ የመጡት ። እኚሁ ነዋሪ ዝርፊያው በአማፅያኑም በመንግሥት ወታደሮችም እንደተካሄደ ነው የሚናገሩት ። በአሁኑ ሰዓት በደቡብ ሱዳን ያሉ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሃገራቸው ለመመለስ በመደረግ ላይ ያለውንም ገልፀውልናል ።

Dina Mufti Sprecher Außenminister Äthiopien
ምስል Getachew Tedla

በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን የሚደርስባቸው ስቃይ ሳያበቃ ከጥቂት ሳምንታት በፊት በየተከሰተው የደቡብ ሱዳን ግጭት ሰላባ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን ለመታገድ የኢትዮጵያ መንግሥት ምን እያደረገ እንደሆነ ተክሌ የኋላ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲን አነጋግሯል።

ግጭት ከተቀሰቀሰበት ከታህሳስ 6 ቀን 2006ዓ,ም ጀምሮም 180 ሺህ የሚሆን ሕዝብ ከቤት ንብረቱ መፈናቀሉን የተመድ አመልክቷል። ዛሬ አማፅያኑ ቦር ከተማን ለመያዝ እየገሰገሱ መሆናቸዉን ሲያመለክቱ የመንግስትኃይሎችም ከባድ ጥቃት እንደሚሰነዝሩ እያስጠነቀቁ ነዉ። በመቶዎች የሚቆጠሩ ኗሪዎችም ሽሽት መጀመራቸዉ ተገልጿል።

ኂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ