1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደቡብ አፍሪቃው የስራ ማቆም አድማ አበቃ

ረቡዕ፣ መስከረም 9 2005

ትንናት በተደረሰው ስምምነቱ መሰረት ሠራተኞቹ ከ 11 እስከ 22 በመቶ የደሞዝ ጭማሪ ይደረገላቸዋል ። በዚህ ሳምንት ሥራ የሚጀምሩ ደግሞ 2 ሺህ ራንድ ተጨማሪ ጉርሻ ያገኛሉ ።

https://p.dw.com/p/16Bbm
Miners sing and dance whilst holding South African bank notes in Lonmin Platinum Mine near Rustenburg, South Africa, Tuesday, Sept. 18, 2012. Striking miners have accepted a company offer of a 22% overall pay increase to end more than five weeks of crippling and bloody industrial action. (Foto:Themba Hadebe/AP/dapd)
ምስል dapd

የደብቡ አፍሪቃው የሎንሚን የፕላቲንየም ማዕድን ማውጫ ሠራተኞች ነገ ወደ ስራ ገበታቸው ለመመለስ ተስማሙ ። ሠራተኞቹ ለሳምንታት የዘለቀውን የሥራ ማቆም አድማ አብቅተው ነገ ወደ ሥራ የሚመለሱት የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄአቸው መልስ በማግኘቱ ነው ። ሰራተኞቹ ፣ የደሞዝ ጭማሪ ስምምነት ላይ በመደረሱ ዛሬ ደሰታቸውን ሲገልጹ ውለዋል ።
6 ሳምንት ያህል የዘለቀው የደቡብ አፍሪቃው የሎንሚን የፕላቲንየም ማዕድን ማውጫ ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ በስምምነት ማብቃቱ ሲነገር ሠራተኞቹ በመዝሙርና በዳንስ ነበር ደስታቸውን በህብረት የገለጹት ። የማዕድን ማውጫው በሚገኝበት በማሪካናው ስታድዮም በሺህዎች የሚቆጠሩ የድርጅቱ ሠራተኞች የደቡብ አፍሪቃን ብሔራዊ መዝሙር ሲዘምሩ ሲስቁና ሲደሰቱ ነው የዋሉት ።
ብዙዎቹ ነገ ሥራ መጀመራቸው አስደስቷቸዋል ። ትንናት በተደረሰው በዚሁ ስምምነቱ መሰረት ሠራተኞቹ ከ 11 እስከ 22 በመቶ የደሞዝ ጭማሪ ይደረገላቸዋል ። በዚህ ሳምንት ሥራ የሚጀምሩ ደግሞ 2 ሺህ ራንድ ተጨማሪ ጉርሻ ያገኛሉ ።

Released mine workers celebrate their release at Ga-Rankuwa Magistrate's Court, Pretoria, South Africa, Monday, Sept. 3, 2012. The miners were among those arrested for public violence after the police opened fire on a group of striking mineworkers killing 34 and wounding 78 at Lonmin's Marikana platinum mine on August 16. Last week, prosecutors said the men arrested would be charged with the murder and attempted murder of their colleagues. Following a public outcry the charges were provisionally withdrawn on Sunday. (Foto:AP/dapd)
ምስል AP


ይህ ጭማሪ ዝቅተኛ ከነበረው ደሞዝ 4500 ራንድ ከፍ ያለ ቢሆንም አስቀድሞ ከጠየቁት 12,500 ራንድ ግን ያንሳል ። የሠራተኖቹ ተወካይ ዞሊሳ ቦድላኒ ምንም እንኳን የተጠየቀውን ያህል የደሞዝ ጭማሪ ባይገኝም ስምምነቱ ተቀብለናል ብለዋል ። ይህን ያደረጉትም የማዕድን አውጭ ሠራተኞች ሥራቸውን እንዳያጡ በሚል ነው ። ሌላው ምክንያት ደግሞ አድማውን ለማስቆም ወታደሮችና ፖሊሶች የሚወስዱትን እርምጃም ለማስቀረት ነው ።
« የመንግሥት እርምጃ አስተዳደሩን የሚያግዝ ነው ። ሊከፋፍሉን ሞክረው ነበር ። ያን ለማስቀረት ወሰን ።ስለዚህ የተሻለው መንገድ የሰጡንን መቀበል ቢያንስ ወደ ሥራ እንመለስ ማንም ከሥራ አይባረርም ማንም ሥራውን አያጣም ። »
የሥራ ማቆም አድማው ሲጀመር በተነሳ ተቃውሞ የ 45 ሰዎች ህይወት መጥፋቱ ይታወሳል ። ከመካከላቸው 34 ቱ በፖሊስ ጥይት ነው ህይወታቸው ያለፈው ። ሌላው የሠራተኞች ተወካይ ጆሴፍ ማቱንጃዋ በሥራ ማቆም አድማው ምክንያት የጠፋውን ህይወት በማስታወስ ስምምነቱ ቀደም ብሎ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ ህይወት ባልጠፋም ነበር ብለዋል ።
«ስምምነቱን ስትመለከት አንድም ህይወት ሳይጠፋ ከ 5 ሳምንት በፊት ሊደረግ ይችል ነበር ። ሆኖም የሆነው ና ያየነው ይህን ነው »

Women carry placards as they chant slogans to protest against the killing of miners by the South African police on Thursday, outside a South African mine in Rustenburg, 100 km (62 miles) northwest of Johannesburg, August 17, 2012.South African Police were forced to open fire to protect themselves from charging armed protesters at the Marikana mine, and 34 of the protesters were killed, Police Commissioner Riah Phiyega said on Friday.She told a news conference that 78 people were injured and 259 arrested in Thursday's violence. "The police members had to employ force to protect themselves from the charging group," Phiyega said. REUTERS/Siphiwe Sibeko (SOUTH AFRICA - Tags: CIVIL UNREST CRIME LAW)
ምስል Reuters


ስምምነቱ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ወገኖች በሙሉ እፎይታን ቢያስገኝም ሌሎች ህገ ወጥ የሥራ ማቆም አድማዎችን ሊያበረታታ ይችላል የሚል ፍራቻ ማስከተሉ አልቀረም ። ቶን ሃርሊ ከሠራተኞች ጋር የተያያዙ ጉዳዮች አማካሪ ናቸው
« እጅግ አስቸጋሪ የነበረ ምዕራፍ መዘጋቱን ሁላችንም እናደንቃለን ። ይህ ምናልባትም ወደፊት አሁን ስምምነት ከተደረሰበትም በላይ ለተጨማሪ የደሞዝ ጥያቄ ህገ ወጥ የሥራ ማቆም አድማዎችን ለማካሄድ መነሻ ሲሆን ልናይ እንችላለን ። ስለዚህ እኔ ይህ ሁለቱንም ወገን በጥሞና የሚያስማማ ሂደት ስለመሆኑ እርግጠኛ አይደለሁም ። »
የሎንሚን ማዕድን ማውጫ ምክትል ፕሬዝዳንት ግን ስምምነቱን ማህበራዊ ሃላፊነት የተሞላበት መፍትሄ ብለውታል ። እዚህ ስምምነት ላይ የተደረሰውም እንደርሳቸው አባባል ድርጅቱንና 28 ሺህ የሥራ ገበታዎችን ለማዳን በህብረተሰቡ ውስጥ የሰፈነውንም ፍርሃት ለማስወገድ ነው ። ይሁንና አሁንም ቢሆንም አንዳንድ ስጋቶች መኖራቸው አልቀረም ። በተለይ ለደሞዝ ጭማሪው ማካካሻ ሠራተኞች ሊቀነሱ ይችላሉ የሚሉ ስጋቶች ይሰማሉ ። ሆኖም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ይህን መሰል እቅድ የለንም ብለዋል ።

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ