1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የደንጉ ትኩሳት በሽታ ሥጋት በድሬዳዋ

ማክሰኞ፣ ጥቅምት 26 2006

ሰሞኑን የድሬደዋ ከተማ ህዝብ የወረርሽኝ በሽታ ሳይገባ አይቀርም በሚል ሥጋት ላይ ይገኛል።በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለታየው በሽታ ምንነት እና ክትትል…

https://p.dw.com/p/1ABvp
Undatiertes Foto einer Tigermücke, die zu den Überträgern des Dengue-Fiebers zählt. Die aus Asien stammende aggressive Mücke sticht auch tagsüber und breitet sich inzwischen in Nordamerika und Europa aus. Foto: Stephan Jansen dpa (zu dpa "Experten: Europa muss gegen gefährliche Moskitos kämpfen" vom 27.09.2012 - Redaktionshinweis: ACHTUNG: DIESER BEITRAG DARF NICHT VOR ABLAUF DER SPERRFRIST, 27. September, 23.00 UHR, VERÖFFENTLICHT WERDEN! DIE NICHTEINHALTUNG DES EMBARGOS HÄTTE EMPFINDLICHE EINSCHRÄNKUNGEN DER BERICHTERSTATTUNG ÜBER WISSENSCHAFTLICHE STUDIEN AUS DEN USA ZUR FOLGE) +++(c) dpa - Bildfunk+++ pixel
ምስል picture-alliance/dpa

ቁጥራቸው ከወትሮው የተለየ ህሙማን በአሁን ሰዓት በድሬደዋ ከተማ መመዝገባቸው ብዙዎችን ስጋት ላይ ጥሏል። የጥቅምትና ህዳር ወር የወባ በሽታ በሰፊው የሚስተዋልበት ጊዜ ቢሆንም ምርመራው ከተደረገላቸው ውስጥ 300 የሚሆኑት ብቻ ናቸው በወባ በሽታ መያዛቸው የተረጋገጠው። በወባ በሽታ ከተያዙ ሰዎች ሌላ ወደ ሁለት ሺ የሚደርሱ ሰዎች በደማቸው ውስጥ የወባ በሽታ አለመገኘቱን የድሬዳዋአስተዳደርጤናቢሮኃላፊ- አቶካሣሁንኃ/ጊዮርጊስ ገልጸዋል።

ለበለጠ ምርመራ ወደ አዲስ አበባ የጤናና ሥነ-ምግብ ምርምር ኢንስቲቱዩት የተላከው ምርመራ እንደሚያሳየው ግን የደንጉ ትኩሳት መሆኑ ሊረጋገጥ ችሏል። በሽታው ከወባ በሽታ ጋ ተመሳሳይ የህመም ምልዕክት እንዳለውም አቶ ካሳሁን ለዶይቸ ቬለ አስረድተዋል።

ትኩሳት ፣ ራስ ምታት እና ነስር የዚህ የደንጉ ትኩሳት ዓይነተኛ ምልክቶች ሲሆኑ እስካሁን በበሽታው የሞተ ሰው እንደሌለ ነው አቶ ካሳሁን የገለፁልን።

ልደት አበበ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ