1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዶቸ ቬለ ሽልማትን ቻይናዊዉ ደራሲ አሸነፈ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 29 2005

ዶቸ ቬለ Bobs ወይም የምርጥ ብሎግ ሽልማት የሚለዉን ሽልማት በመላዉ ዓለም ከሚገኙ የአምደ መረብ አምደኞች አወዳድሮ ይሸልማል።የዘንሮዉን ሽልማት ያሸነፈዉ ሊ ብሎገር፥ ደራሲና ሐያሲ ነዉ።

https://p.dw.com/p/18Tgf
Chinese writer Li Chengpeng, looked upon by many as a a highly influential Chinese blogger and social commentator, attends a promotional event of his new book "SmILENCE" on January 26, 2013 in Kunming, southwest China's Yunnan province. Li was attacked by Maoists earlier at his book signings in Beijing and Shenzhen, forcing him to cancel two others in Guangzhou and Changsha. The Maoists take offence to Li's caustic essays and comments about the Communist Party?s governance. Li has previously been punched in the head at a previous signing. CHINA OUT AFP PHOTO (Photo credit should read STR/AFP/Getty Images)
የዘንድሮዉ ተሸላሚ ሊምስል AFP/Getty Images

ዶቸ ቬለ ለአምደ መረብ-ፀሐፊዎችና ዓምደኞች በየዓመቱ ከሚሠጠዉ ሽልማት የዘንድሮዉን (2013)ቻይናዊዉ አምደኛ እና ደራሲ ሊ ቼንግፔንግ አሸነፈ።ዶቸ ቬለ Bobs ወይም የምርጥ ብሎግ ሽልማት የሚለዉን ሽልማት በመላዉ ዓለም ከሚገኙ የአምደ መረብ አምደኞች አወዳድሮ ይሸልማል።የዘንሮዉን ሽልማት ያሸነፈዉ ሊ ብሎገር፥ ደራሲና ሐያሲ ነዉ።ሸላሚዎቹ ዳኞች እንዳሉት የመንግሥትን አሠራሮች በመተቸት የሚታወቀዉ ሊ ከሐገሩ ዜጎች በተለይም ከወጣቶቹ ከፍተኛ ዝናንና አድናቆትን ያተረፈ ነዉ።የሊ ብሎግ ከሰባት ሚሊዮን በላይ አባላት አሉት።የዶቸ ቬለዋ የቋቋዎች አገልግሎት ሐላፊ ወይዘሮ ኡተ ሼፈር እንደሚሉት ደግሞ ሊን የመሳሰሉ ወጣቶች በንቃት የሚሳተፉበት የአምደ መረብ አገልግሎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና እያደገ ነዉ።

              
«ቦብስ 2013 ያሳየን፥ የአምደ መረብ እንቅስቃሴ ማለት የአምደ-መረብ ፖለቲካዊ እና ማሕበራዊ ሥራ መቀየሩን ነዉ።እንቅስቃሴዎቹና ተሳታፊዎቹ ፈጣሪዎች፥ተንቀሳቃሳሾች፥ሁሉን መገናኛ ዘዴዎች ያሰባጠሩ፥ በቴክኒክ ረገድም ባለ ብዙ ገፅታ ሆነዋል።ይሕ ማለት መልክና ቅርፃቸዉ ተቀይሯል ማለት ነዉ።በዚሕ ዓመት ለፕሮጀክታችን በጣም ከፍተኛ የሆነ ጉጉት አይተናል።ይሕ የሚያሳየዉ የአምደ መረብ ንቅናቄ በመላዉ ዓለም ምን ያሕል ተፈላጊ እንደሆነ ነዉ።»

ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ድንበር የለሽ ዘጋቢዎች ደግሞ የዘንድሮዉን የአምደ መረብ ሽልማቱን ለቶጎዊቷ ጋዜጠኛ ለ ፋቢ ኮሚሲ ሰጥቷል።ጋዜጠኛ ፋቢ የቶጎ ጋዜጠኞች የሚደርስባቸዉን ግፍና በደል በአምደ መረቧ በማጋለጥና የመንግሥትን የሐይል እርምጃ በመተቸት የታወቀች ጋዜጠኛ ነኝ።
              
«ብሎጌ ከሁሉም በላይ የቶጎ ጋዜጠኞች ያሉበትን ሁኔታ የሚያንፀባርቅ ነዉ።ፕሬሱ እዚሕ ከፍተኛ ችግር አለበት።እኛ ሐገር ዲሞክራሲ የለም።ይሕን ብሎጎ መምራት ከጀመርኩ ጥቂት ዓመታት ሆኖኛል።የዶቸ ቬለን ትኩረት ያገኛል ብዬ አስቤ ግን አላዉቅም ነበር።በጣም ተደስቻለሁ፥ ኮርቻለሁም።»

ትላለኝ ፋቢ።የዶቸ ቬለ ለምርጥ ማሕበራዊ እንቅስቃሴ፥ ለምርጥ ፈጠራ፥ እና ለምርጥ የጀርመንኛ ቋንቋ ብሎግም የቦብስ ሽልማትን ሰጥቷል።

ነጋሽ መሐመድ

The Bobs, Jury Mitglieder am 5.5.2013 in der Deutschen Welle Berlin.
ዳኞቹምስል DW/Jan Röhl
Copyright : Naji Tbel Gewinner von The Bobs Die DW würdigt in der Kategorie Best Social Activism das Engagement von Menschen in Sozialen Medien zur Stärkung von Demokratie und Menschenrechten. Hier siegte die marokkanische Jugendinitiative 475 – www.facebook.com/475LeFilm. Sie richtet das Augenmerk auf das Schicksal vergewaltigter Frauen
የምርጥ ማሕበራዊ እንቅስቃሴ ተሸላሚዎችምስል Naji Tbel

ልደት አበበ