1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመንና የብራዚል የግማሽ ፍፃሜ ግጥምያ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 1 2006

በአጓጊነቱ የቀጠለዉ ብራዚል ላይ እየተካሄደ ያለዉ የዓለም የእግር ኳስ ግጥምያ ዛሬ በአስተናጋጅ ሀገር ብራዚል እና በጀርመን መካከል ጀምሮአል። ግጥምያዉ በጀርመን በጉጉት እየተጠበቀ ነዉ

https://p.dw.com/p/1CYMw
Halbfinale WM Brasilien - Deutschland Fans Vorfreude Fahne
ምስል Reuters

በግማሽ ፍፃሜው ላቲን አሜሪካዉያኑ ሁለት ሀገራትና ከመሃል አዉሮጳ ሁለት ሀገር ለግጥምያ በመቅረባቸዉ ዉድድሩን ለየት አድርጎታል።
ባለፈዉ ሳምንት መጠናቀቅያ ላይ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለመግባት የተጋጠሙት አርጀንቲና እና ቤልጂየም አንድ- ለባዶ መለያየታቸዉ ይታወሳል ። የአርጀንቲናዉ ጎንዛሎ ሂጎይን ስምተኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ቡድኑን ወደ ግማሽ ፍፃሜ አድርሶታል። አምስት ሰዓት ላይ የተጋጠሙት ሆላንድና ኮስታሪካ ለግማሽ ፍጻሜዉ መለያ መደበኛ የግጥምያ ሰዓታቸዉን አጠናቀዉ በፍፁም ቅጣት ሆላንድ 4 ለ 3 በማሸነፍ ለቀጣይ ዉድድር ቡድኑን የተቀላቀለዉ። በዚህም በግማሽ ፍፃሜው ላቲን አሜሪካዉያኑ ከአዉሮጳዉያኑ ሀገራት ጋር ይጋጠማሉ። ዛሪ ማክሰኞ ጀርመን ከዓለም ዋንጫ ዉድድር አዘጋጅዋ ከብራዚል፤ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 5 ሰዓት ፤ ነገ ረቡዕ ደግሞ ሆላንድ ከአርጃንቲና ለፍፃሜዉ ለማለፍ ይተናነቃሉ።የብራዚልና የጀርመን ብሄራዊ የእግርኳስ ቡድን እንዴት ይገመገማል በቼክ ሪፐብሊክ የአንድ ከተማ የእግር ኳስ አስልጣኝ የሆኑት ዶክተር ተስፋዬ ጥላሁንን ስቱድዮ ከመግባታችን በፊት አነጋግረናቸዉ ነበር።


አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ