1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን ምክር ቤት የኮምፕዩተር ስለላ

ሐሙስ፣ ሰኔ 4 2007

የጀርመን ምክር ቤት ማለትም ቡንደስታኽ ላይ የደረሰዉ የሳይበር ማለትም የኢንተርኔት መረጃ ዘረፋ ጥቃት ቀደም ሲል ከተገመተዉ በላይ ጠንከር ያለ ጉዳት ሳያደርስ እንዳልቀረ እየተነገረ ነዉ።

https://p.dw.com/p/1FfrM
Symbolbild Cyberangriff auf den Bundestag
ምስል picture-alliance/dpa/R. Jensen

[No title]

የሀገሪቱን የመገናኛ አዉታሮች የሚጠብቀዉ ክፍል ከእንግዲህ እንዲህ ያለዉን የሳይበር ጥቃት መክቶ መከላከሉን አቁሞ ኮምፕዩተሮቹን ጠቅላላ ነቅሎ በአዲስ ተክቶ ፕሮግራሞችንም በሌላ መተካት ይገባል ከሚል ዉሳኔ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። ዛሬ በርሊን ላይ እንደተነገረዉ የጀርመን ሸንጎ አባሎችና የመሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች ምስጢርና ሰነድ መጠለፉ አስቀድሞም ተደርሶበት ነበር። ከጀርባዉ ትልቅ የስለላ ድርጅት ስለመኖሩ ከመነገሩ ዉጭ ግን ማንነቱም ሆነ የደረሰዉ የጥፋት መጠን በሰፊዉ አልታወቀም። ይልማ ኃይለሚካኤል ከበርሊን ዝርዝር ዘገባ አለዉ

ይልማ ኃይለሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ