1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን የልማት ትብብር ሚኒስትር ጉብኝት በኢትዮዽያ

ዓርብ፣ ጥር 6 2003

የጀርመን የልማት ትብብር ሚኒስትር ደርክ ኒብል በኢትዮዽያ የአራት ቀናት ጉብኝታቸውን የጀመሩት ባለፈው ማክሰኞ ነበር።

https://p.dw.com/p/QsWd
ምስል picture alliance/dpa

በተለያዩ የልማት ድርጅቶች የተከናወኑ ስራዎችን የተመለከቱት ኒብል ወደ ኢትዮዽያ ከማምራታቸው በፊት በኢትዮዽያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ የነጻው ፕሬስ የመታፈን ጉዳይ ላይ ከኢትዮዽያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር እንደሚነጋገሩ መግለጻቸው ይታወሳል። ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ወቅት የሰብዓዊ መብቱን ጉዳይ አጽንኦት ሰጥተው እንዲመለከቱት የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሲጎተጉቱ ሰንብተዋል። ሚኒስትር ኒብል ዛሬ ጉብኝታቸውን አጠናቀዋል። ጌታቸው ተድላ ሃይለጊዮርጊስ አነጋግሮዋቸው ነበር።

መሳይ መኮንን

ተክሌ የኋላ