1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን የነጻ ትምህርት እድል

ሰኞ፣ ሚያዝያ 17 2008

የጀርመን መንግሥት በሦስት የአፍሪቃ ሃገራት በመሬት አስተዳደርና ፖሊሲ ትምህርት የሦስተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር የነፃ ትምህርት እድል እንደሚሰጥ አስታወቀ ።

https://p.dw.com/p/1IcLB
Äthipoien Start deutsch äthiopische Forschungsprojekte in Addis Ababa
ምስል DW/Y. Gebereegeziabeher

ባለፈዉ ሃሙስ አዲስ አበባ ዉስጥ በተካሄደዉ ሥነ-ስርዓት ላይ፤ በኢትዮጵያ በባሕርዳር ዩንቨርስቲ እንዲሁም በናሚቢያና ታንዛንያ በሚገኙ ዩንቨርስቲዎች በሚሰጡ የ «ፒ ኤች ዲ» ፕሮግራሞች አንድ መቶ አፍሪቃዉያን ተጠቃሚዎች እንደሚሆኑ ተነግሮአል። በዚህ መድረክ ላይ ተገኝተዉ የነፃ ትምህርት እድሉን ይፋ ያደረጉት የጀርመን የኢኮኖሚ ትብብርና የልማት ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር ቶማስ ሲልበርሆርን በሦስቱ ሃገራት ዩንቨርስቲዎች ለዶክትሪት ዲግሪያቸው ለሚማሩ አፍሪቃዉያን የትምህርትና የቀለብ ሙሉ ወጫቸዉን የሚችለዉ የጀርመን መንግሥት እንደሚሆንም አስታውቀዋል። ዝግጅቱ ላይ የተገኘዉ የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮኃንስ ገብረግዚአብሄር ዘገባዉን ልኮልናል።

ዮኃንስ ገብረግዚአብሄር

አዜብ ታደሰ

ሒሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ