1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጀርመን የጦር መሣሪያ ለኩርዶች

ሰኞ፣ ነሐሴ 26 2006

ኢራቅ ዉስጥ ለሚገኙ የኩርድ ተወላጆች የጦር መሣሪያ እናቅርብ የሚለዉ ሃሳብ ባለፉት ሳምንታት እዚህ ጀርመን ሲነሳ ሁለት የተለያዩና የሚፃረሩ አስተያየቶች ባለፉት ቀናት ተሰምተዋል። በእነዚህ ነጥቦች ላይም ሰሞኑን ፖለቲከኞቹ ሲከራከሩበት ሰንብተዋል።

https://p.dw.com/p/1D4r1
Pressekonferenz von der Leyen Steinmeier zu Waffenlieferungen an irakische Kurden
ምስል Odd Anderson/AFP/Getty Images

አንደኛዉ ወገን ኩርዶችን በጀርመን የጦር መሣሪያ ማስታጠቅ አደጋ አለዉ ሲል ሌላዉ ወገን በበኩሉ እነሱን ማስታጠቅ በመካከለኛዉ ምሥራቅ የእስልምና መንግሥታትን እንመሠርታለን የሚሉትን ሽብር ፈጣሪዎች እዚያዉ እንዋጋለን የሚለዉን ምላሽ ሰጥቷል። የጀርመን የጣምራ መንግሥትም በዚሁ የጦር መሣሪያ ለኩርዶች እንስጥ በሚለዉ ሃሳብ ተስማቷል። የበርሊኑ ወኪላችን ይልማ ኃይለሚካኤል ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ሸዋዬ ለገሠ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ