1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጃፓን እና የቻይና መሪዎች ጉብኝት በኢትዮጵያ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 30 2006

የጉብኝቱ መርኃ ግብር እንደሚያመለክተው የጃፓኑ ጠ/ሚ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ኢትዮጵያን ይጎበኛሉ። ከሳቸው ቀደም ብለው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትራቸው አዲስ አበባ እንደሚገቡ የተገለጸ ሲሆን የጉብኝታቸው ዓላማም የጠ/ሚ ሺንዞ አቤን ጉብኝት ከወዲሁ ለማዘጋጀት ነው ተብሏል።

https://p.dw.com/p/1AnA6
Karte Äthiopien englisch

አቤ ከኢትዮጵያ በተጨማሪም ሞዛንቢክን፣ ኣይቮሪኮስትን እና ወደ ማዕከላዊው ምስራቅ ተሻግረው ደግሞ ኦማንን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተለይም ማፑቶ ላይ ለሞዛንቢክ የ 577 ሚሊየን የን ብድር ይፈቅዳሉ ተብለው የሚጠበቁት ኣቤ ለኢትዮጵያም ቢሆን ለእንፋሎት ኃይል ማመንጫ የሚውል የ 10 ቢሊየን የን ብድር እንደሚፈርሙ ለማወቅ ተችሏል። የኣሁኑ የጃፓን መሪዎች ጉብኝት ተንታኞች እንደሚሉት በጥሬ ኃብት ኣቅርቦት በበለጸገችው ኣፍሪካ በፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውን የቻይናን እንቅስቃሴ ለመጋፈጥ ነው ተብሏል።

Japan Gedenken an Atombombenabwurf 1945 Premier Abe
ምስል picture alliance/Kyodo

የቻይናው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርም በዚህ ሳምንት አዲስ አበባ መሰንበታቸው ሲታወቅ የሁለቱ ኣገሮች መሪዎች በተመሳሳይ ሳዓት ኢትዮጵያን መጎብኘት በመካከላቸው ያለው የኢኮኖሚ ፉክክር በተለይም ኣፍሪካን ኣስመልክቶ እየተካረረ መምጣቱን እንደሚያመለክት ብዙዎች ይገምታሉ።

የኢትዮጵያው ጠ/ሚ ቃ/ኣቀባይ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ግን ኣስቀድሞ የተያዘ ፕሮግራም በመሆኑ የሁለቱ ተቀናቃኝ ኣገሮች መሪዎች ጉብኝት መገጣጠሙ የኣጋጣሚ ጉዳይ ነው ይላሉ።

APEC Bali Chinas Präsident Xi Jinping
ምስል Reuters

በኢትዮጵያ የቢዝነስ ህክምና ተቐም መስራች የሆኑት፣ የኢኮኖሚ ባለሙያው፣ አቶ ኣህመድ ባቶሌ በበኩላቸው የቻይና ፈጣን ግስጋሴ ከጃፓንም ኣልፎ ምዕራባውያንንም ጭምር እያሳሰበ መቷል ይላሉ።

ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ታሪካዊ ጠባሳ ወዲህም ቢሆን በአካባቢያቸው በደሴት ይገባኛል ጥያቄ የሚወዛገቡት ጃፓን እና ቻይና በኢኮኖሚ ፉክክርም ገላጋይ የታጣላቸው ባላንጣዎች እየሆኑ ከመጡ ውለው ኣድሯል። በተለይም ቻይና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በምታደርገው ፈጣን ግስጋሴ ጃፓንን ከገበያ እየገፋች በመምጣቷ የኣሁኑ የቶኪዮ መፍጨርጨርም የትርፍ ብቻም ሳይሆን ተንታኞች እንደሚሉት የህልውና ጉዳይም ጭምር ነው ተብሏል።

ጃፈር ዓሊ

ኣርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ