የገንዘብ ማጭበርበር ቅሌት26 መጋቢት 2008ሰኞ፣ መጋቢት 26 2008በጣም ብዙ የሀገር መሪዎች፣ ንጉሣዊ ቤተሰቦች፣ ፖለቲከኞች፣ ግብር እንዳይከፍሉ ሲሉ ገንዘባቸውን ወደ ፓናማ በድብቅ ማሸሸታቸው ተጋለጠ። ስማቸው ከዚሁ ቅሌት ጋር ተያይዞ የተጠቀሱት ታዋቂ ሰዎች ገንዘባቸውን መንበሩን ፓናማ ባደረገው «ሞሳክ ፎኔስካ» በተባለ ድርጅት ስር በከፈቱት የሽፋን አድራሻ ማስቀመጣቸው ነው የተሰማው።https://p.dw.com/p/1IP98ምስል DW/B. Klingማስታወቂያ[No title]To play this audio please enable JavaScript, and consider upgrading to a web browser that supports HTML5 audio ገንዘባቸውን በድብቅ አሸሽተው በፓናማ አስቀምጠዋል ከተባሉት መካከል በስፖርት እና በሌሎች ዘርፎች የታወቁ ግለሰቦች እና ሕገ ወጥ የእፅ ነጋዴዎችም ይገኙባቸዋል። ይህንን ያጋለጠው ከአንድ መቶ በላይ ከሆኑ ጋዜጠኞች ጋር በመተባበር የአንድ ዓመት ምርመራ ያካሄደው የጀርመናውያኑ ዕለታዊ «ዚውድዶይቸ» ጋዜጣ ነው። ይልማ ኃይለሚካኤል አርያም ተክሌ አዜብ ታደሰ