የጋምቤላዉ ተፈናቃይ ክስ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 24 2006ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎች ከቤት ንብረቴ አፈናቀሉኝ፥ አሠሩኝ፥ ደበደቡኝም ያሉ አንድ የጋምቤላ መስተዳድር ነዋሪ የኢትዮጵያን መንግሥት ይደግፋል ያሉትን የብሪታንያ መንግሥትን ከሰሱ።ሥማቸዉ ለደሕንነታቸዉ ሲባል በሚስጥር የተያዘዉ ኢትዮጵያዊ በጠበቆቻቸዉ በኩል የመሠረተቱትን ክስ የብሪታንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትናንት ማድመጥ ጀምሯል።ከሳሽ እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በሠፈራ መርሐ-ግብሩ በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማፈናቀል፥ ማሰደዱን የብሪታንያ መንግሥት እያወቀ ለኢትዮጵያ መንግሥት በተለይም ለፀጥታ አስከባሪዎች ማሰልጠኛ ርዳታ መስጠቱ ለተፈፀመዉ በደል አባሪ ተባባሪ መሆኑን አመልካች ነዉ።የለንደኑ ወኪላችን ድልነሳ ጌታነሕ አጭር ዘገባ ልኮልናል።
ድልነሳ ጌታነሕ
ነጋሽ መሐመድ
ተክሌ የኋላ