የግሪክ ምርጫ ውጤትና አንድምታው
ሰኞ፣ መስከረም 10 2008ማስታወቂያ
ትናንት በተካሄደው የግሪክ ምክር ቤታዊ ምርጫ ፣ለሁለተኛ ጊዜ ያልተጠበቀ ድል ያገኙት የግሪክ ግራ ፓርቲዎች ጥምረት ሲሪዛ ፓርቲ መሪ አሌክሲስ ሲፕራስ ዛሬ (ማምሻውን) ቃለ መሀላ ፈፅመዋል ።(ይፈፅማሉ )ተብሎ ይጠበቃል ። በትናንቱ ምርጫ 35.5 በመቶ ድምጽ በማግኘት ያሸነፈው ፓርቲያቸው ሲሪዛ «ነፃይቱ ግሪክ» በአህፅሮቱ Anel ከተባለው ፓርቲ ጋር ተጣምሮ መንግሥት እንደሚመሰርት ተገልጿል ። በእሁዱ ምርጫ ወግ አጥባቂው «አዲስ ዲሞክራሲ »28.1 በመቶ ድምፅ በማግኘት ሁለተኛውን ደረጃ ይዟል ።የናዚ አስተሳሰብ የሚያራምደው «ጎልድን ዶውን» የተባለው ፓርቲ 7 በመቶ ድምፅ በማሸነፍ 3ተኛ ደረጃ አግኝቷል ። የአውሮፓ ህብረት ለሲፕራስ የእንኳን ደስ አለዎ መልዕክቱን አስተላልፎ ፣ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያገኙትን ሥልጣን ባለፈው ነሐሴ የተስማሙበትን የ3 ዓመት የብድርና መርሃ ግብር ተግባራዊ ለማድረግ እንዲጠቀሙበት አሳስቧል ። በእሁዱ ምርጫ ከ10 ግሪካውያን ከ4 በላይ የሚሆኑት ድምጻቸውን እንዳልሰጡ ተዘግቧል ።ስለ ግሪክ ምርጫና አንድምታው የብራሰልሱ ወኪላችን ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል ።
ገበያው ንጉሴ
ኂሩት መለሰ
አርያም ተክሌ