1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግብፅ ምርጫ እና የተከተለው ተቃውሞ

ማክሰኞ፣ ግንቦት 21 2004

በግብፅ የመጀመሪያው ዙር ፕሬዚደንታዊው ምርጫ ውጤት ትናንት ይፋ ሆኖዋል። በምርጫው ውጤት መሠረት፡ የሙስሊም ወንድማማችነት ፓርቲ ዕጩ መሀመድ ሙርሲ 24,3 ከመቶ ፡ የቀድሞ የግብፅ ፕሬዚደንት ሆስኒ ሙባራክ ዘመን ጠቅላይ ሚንስትር የነበሩትን

https://p.dw.com/p/1549L
Source News Feed: EMEA Picture Service ,Germany Picture Service Protesters wave their shoes during a protest against presidential candidates Mohamed Mursi and Ahmed Shafiq at Tahrir square in Cairo May 28, 2012. Egypt will hold a run-off next month in its first truly contested presidential election in which the Muslim Brotherhood's Mursi will face Shafiq, the last prime minister of deposed leader Hosni Mubarak. REUTERS/Suhaib Salem (EGYPT - Tags: POLITICS ELECTIONS CIVIL UNREST)// eingestellt von se
ምስል Reuters

የአህመድ ሻፊቅ ደግሞ 23,3 ከመቶ የመራጩን ድምፅ በማግኘት የፊታችን ሰኔ አጋማሽ ለሁለተኛ ዙር ምርጫ ይወዳደራሉ። ይህ ይፋ ከተነገረ በኋላ በአሌግዛንድርያ፡ በፖርት ሰይድ፡ በኢዝማይሊያ እና በስዌዝ ከተሞች የኃይል ርምጃ የታከለበት ተቃውሞ ተካሂዶዋል። በተለይ በመዲናይቱ ካይሮ የታህሪር አደባባይ የወጡ ወደ ሁለት ሺህ የሚጠጉ ተቃዋሚዎች የአህመድ ሻፊቅ የምርጫ ጽሕፈት ቤት ማዕከልን በእሳት አጋይተዋል። በዚሁ ጊዜም ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋ ግጭት ቢፈጠርም፡ ቀደም ሲል የጄዳው ወኪላችን ነቢዩ ሲራክ በስልክ እንደገለጸልን፡ በወቅቱ ሁኔታው የተረጋጋ ይመስላል።


ነቢዩ ሲራክ
አርያም ተክሌ
ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ