1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግብፅ ወቅታዊ ሁኔታና ዓለም አቀፍ አስተያየት፣

ሐሙስ፣ ነሐሴ 9 2005

ግብጽ ውስጥ ትናንት የተወሰደውን የኃይል እርምጃ፤ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በጥብቅ ነው ያወገዘው።

https://p.dw.com/p/19QeH
ምስል Mahmoud Khaled/AFP/Getty Images

በግብፅ ፣ የሽግግሩ መስተዳድር ፀጥታ አስከባሪ ኃይሎች ፣ ከሥልጣን የተወገዱት ፕሬዚዳንት ሙሐመድ ሙርሲ ደጋፊዎች ፣ ካይሮ ውስጥ በከተማይቱ አንዳንድ አደባባዮች ከመሸጉባቸው ጣቢያዎች እንዲለቁ ለማስገደድ በወሰዱት እርምጃ የብዙ ሰዎች ሕይወት መጥፋቱ እንደታወቀ፤ የአፍሪቃ ኅብረት የሰላምና ፀጥታ ኮሚሽን፤ ያቋቋመውን አጥኚ ቡድን ፤ በአፋጣኝ ልኳል። የግብፅን ወቅታዊ ይዞታ በተመለከተ፣ በዚያው በአፍሪቃ ኅብረት ምክክር መደረጉም ታውቋል።

Ägypten Tag nach den Ausschreitungen 15. August 2013
ምስል picture-alliance/AP Photo

ትናንት ፣ የግብፅ ፖሊስና ወታደር 12 ሰዓት ያህል በወሰደው የኃይል እርምጃ እንደ ሙስሊም ወንድማማች ማኅበር መግለጫ ከሆነ ከ 2,000 በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በሺ የሚቆጠሩ ደግሞ ቆስለዋል።የሽግግሩ መንግሥት በበኩሉ፤ 43 ፖሊሶች እንደተገደሉበት ያስታወቀ ሲሆን፤ ገለልተኛ የዜና አውታሮች፣ ቢያንስ ከ 250 በላይ ተገድለዋል ይላሉ። ባሁኑ ወቅትም፣ በካይሮና በሌሎች 11 ከተሞች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የወጣ ሲሆን የሰዓት እላፊ ገደብም ተጥሏል። ከአካባቢው የሚገኙ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ሁኔታው አስፈሪና አሳሳቢ ነው።


ጌታቸው ተድላ ኃ/ጊዮርጊስ/ገበያው ንጉሤ

ተክሌ የኋላ

ሂሩት መለሰ