1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጎሳ ግጭት በአፋር

ዓርብ፣ ሚያዝያ 2 2007

የዓይን ምስክር በግጭቱ ከ10 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል ። የዓይን ምስክሩ እንደሚሉት ግጭቱ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል ። የግጭቱ መንስኤ የግጦሽ ቦታ ይገባኛል ጥያቄ መሆኑን ተነግሯል ።

https://p.dw.com/p/1F65g
Äthiopien Landschaft in Provinz Afar Kamele durch die Wüste
ምስል picture-alliance/dpa

በአፋር ክልል በአሚባራ ወረዳ ቦልሃም በተባለ ቦታ በሁለት ጎሳዎች መካከል በተነሳ ግጭት የሰዎች ህይወት አለፈ ። ዘጋቢያችን ዮሀንስ ገብረ እግዚአብሄር ያነጋገራቸው የዓይን ምስክር በግጭቱ ከ10 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል ። የዓይን ምስክሩ እንደሚሉት ግጭቱ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል ። የግጭቱ መንስኤ የግጦሽ ቦታ ይገባኛል ጥያቄ መሆኑን ተነግሯል ። በአፋርና በሌሎችም አካባቢዎች የሚነሱ መሰል ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ባህላዊ የግጭት አፈታት ዘዴንና ዘመናዊ ህግን አጣምሮ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ዶቼቬለ ያነጋገራቸው አንድ የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ተናግረዋል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሄር

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ