1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ስንብትና የቀብር ስነ ስርዓት

ዓርብ፣ ነሐሴ 25 2004

የአቶ መለስ የቀብር ስነሥርዓት እሑድ በመንበረ ጸባኦት ቅድሥት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን እንደሚፈፀምና የውጭ ሃገራት መሪዎች ንግግርና የስንብቱ ስነ ስርዓት ደግሞ በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ዲና ሙፍቲ ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ።

https://p.dw.com/p/161hE
Meles Zenawi, Prime Minister of Ethiopia, speaks during the conference 'Energy for All' in Oslo, Norway Monday Oct. 10, 2011. U.N. Secretary-General Ban Ki-moon has called for making electricity available to all by 2030 saying energy poverty threatens global economic growth and the creation of jobs. Ban says that a clean energy revolution is needed that would double the use of renewable energy sources in 20 years.(Foto:Erik Johansen/Scanpix Norway/AP/dapd) NORWAY OUT
ምስል dapd

የፊታችን እሁድ ነሐሴ 27 2004 ዓም የቀብር ስነ ስርዓታቸው ለሚፈፀመው ለኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በተለያዩ ደረጃዎች ስንብት እየተካሄደ ነው ። ከትናንት አንስቶም የየማህበረሰቡ ተወካዮች በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ በመገኘት ሻማ ና ጧፍ በማብራት ሃዘናቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው ። በአፍሪቃ ህብረትም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሃዘን መግለጫ ስነ ስርአት ተካሂዷል ። የአቶ መለስ የቀብር ስነሥርዓት እሑድ በመንበረ ጸባኦት ቅድሥት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን እንደሚፈፀምና የውጭ ሃገራት መሪዎች ንግግርና የስንብቱ ስነ  ስርዓት ደግሞ በመስቀል አደባባይ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ዲና ሙፍቲ ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ። ዝርዝሩን የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ አዘጋጅቶታል ።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ

ሂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ