1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፔጊዳ ሰልፍ መታገድ

ሰኞ፣ ጥር 11 2007

ፖሊስ ደርሶኛል ባለው መረጃ ምክንያት የድሬስደኑ ሰልፍ ቢገፋም በሌሎች የጀርመን ከተሞች ግን ፔጊዳ የጠራቸው ሰልፎች ይካሄዳሉ ።

https://p.dw.com/p/1EMlH
Pegida Demonstration Polizei Sicherheit Terrorgefahr Absage
ምስል picture-alliance/dpa/A. Burgi

ፔጊዳ የተባለው በአውሮፓ የእሥልምናን መስፋፋት እቃወማለሁ የሚለው ንቅናቄ ለዛሬ በምሥራቅ ጀርመንዋ በድሬስደን ከተማ ሊያካሂድ ያቀደው ሰልፍ መታገድ እዚህ ጀርመን እያነጋገረ ነው ። የፔጊዳ ሰልፍ ብቻ ሳይሆን በከተማይቱ ዛሬ ፔጊዳን በመቃወም ሊካሄድ የታሰበው የአደባባይ ሰልፍና ሌሎችም ህዝባዊ ስብሰባዎች መታገዳቸው ድጋፍም ተቃውሞም ገጥሞታል ። ፖሊስ ደርሶኛል ባለው መረጃ ምክንያት የድሬስደኑ ሰልፍ ቢገፋም በሌሎች የጀርመን ከተሞች ግን ፔጊዳ የጠራቸው ሰልፎች ይካሄዳሉ ። ስለ እገዳውና በእገዳው ላይ ስለሚሰነዘሩ አስተያየቶች የበርሊኑን ዘጋቢያችንን ይልማ ኃይለ ሚካኤልን ኂሩት መለሰ በስልክ አነጋግራዋለች ።

ይልማ ኃይለ ሚካኤል

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ