የፔጊዳ ሰልፍ መታገድ
ሰኞ፣ ጥር 11 2007ማስታወቂያ
ፔጊዳ የተባለው በአውሮፓ የእሥልምናን መስፋፋት እቃወማለሁ የሚለው ንቅናቄ ለዛሬ በምሥራቅ ጀርመንዋ በድሬስደን ከተማ ሊያካሂድ ያቀደው ሰልፍ መታገድ እዚህ ጀርመን እያነጋገረ ነው ። የፔጊዳ ሰልፍ ብቻ ሳይሆን በከተማይቱ ዛሬ ፔጊዳን በመቃወም ሊካሄድ የታሰበው የአደባባይ ሰልፍና ሌሎችም ህዝባዊ ስብሰባዎች መታገዳቸው ድጋፍም ተቃውሞም ገጥሞታል ። ፖሊስ ደርሶኛል ባለው መረጃ ምክንያት የድሬስደኑ ሰልፍ ቢገፋም በሌሎች የጀርመን ከተሞች ግን ፔጊዳ የጠራቸው ሰልፎች ይካሄዳሉ ። ስለ እገዳውና በእገዳው ላይ ስለሚሰነዘሩ አስተያየቶች የበርሊኑን ዘጋቢያችንን ይልማ ኃይለ ሚካኤልን ኂሩት መለሰ በስልክ አነጋግራዋለች ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ኂሩት መለሰ