1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፖሊስ የግድያ ርምጃ በቺካጎ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 21 2008

ዛሬ በሚገባደደው የፈረንጆቹ 2015 ብቻ በዩናይትድስቴትስ 1000 የሚጠጉ ግለሰቦች በፖሊስ ጥይት ተገድለዋል።

https://p.dw.com/p/1HWdb
Polizeiabsperrung nach tödlichen Schüssen auf zwei Afroamerikaner in Chicago
ምስል picture-alliance/AP Photo

[No title]

ባለፈው የፈረንጆች የገና በአል ማግስት በኢሊኖይስ ግዛት ችካጎ ከተማ አንድ የ19 አመት ወጣትና የ55 አመት ወይዘሮ በፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መገደላቸውን ተከትሎም የከተማዋ ከንቲባ ከስልጣናቸው እንዲለቁ የሚጠይቁ ሰልፈኞች በርክተዋል። ከንቲባ ራም ኢማኑኤል የሰልፈኞቹን ጥያቄ ወደጎን በመተው ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስተዳደራቸው በከተማዋ ፖሊስና በህብረተሰቡ መካከል የተፈጠረውን አለመተማመን ሊቀርፍ የሚችል አዲስ ፖሊሲ ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ናትናኤል ወልዴ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ሸዋዬ ለገሰ