የ16ተኛው ዓ/ዓቀፍ የኤች አይ ቪ ኤድስ እና የአባለዘር በሽታዎች ጉባኤ ፍፃሜ
ዓርብ፣ ኅዳር 29 2004ማስታወቂያ
ወደ 10 ሺህ የሚጠጉ ተሳታፊዎችን ባስተናገደው በዚሁ ጉባኤ ላይ በርካታ የምርምር ፅሁፎች ቀርበው ውይይቶችም ተካሂደዋል ። ለ ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያ እና ህክምና ከለጋሽ ሃገራት የሚገኘው ገንዘብ እየቀነሰ የመሄዱ ስጋት የጉባኤው አንዱና ዋነኛ የመነጋገሪያ ርዕስ ነበር ። ከሰራ በታች በሚገኘው የአፍሪቃ ክፍል ብቻ 22.9 ሚሊዮን ሰዎች ከ ኤች አይ ቪ ኤድስ ጋር በሚኖርባት በአፍሪቃ ለኤድስ መድኃኒት እና ህክምና የሚያስፈልገው ገንዘብ እጅግ ከፍተኛ በሆነበት በአሁኑ ወቅት ለችግሩ ብልሃት ማፈላለጉ አብይ ትኩረት ተሰጥቶታል ። ጉባኤው ስለተነጋገረባቸው ጉዳዮች ሂደቱን ሲከታተል የቆየውን የአዲስ አበባውን ወኪላችንን ታደሰ እንግዳውን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።
ታደሰ እንግዳው
ሂሩት መለሰ