1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ደራሲ መሥፍን ተቀበረ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 8 2006

መስፍን ሐብተማርያም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ የወግ ፀሐፊ ነበር።በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ወጎችን የፃፈና ያሳተመ፤ ተርጓሚ፤ የሥነ-ፅሁፍ ሐያሲ እና አዲስ አበባና አሥመራ ዩኒቭርስቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ያስተማረ የሥነ-ፅሁፍ ሰዉ ነበር።

https://p.dw.com/p/1CdYO
ምስል DW/J. Egziabhare

 

ኢትዮጵያዊዉ ደራሲ፤ሐያሲና መምሕር መሥፍን ሐብተማርያም ዛሬ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን አዲስ አበባ ዉስጥ ተቀበረ።መስፍን ሐብተማርያም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ የወግ ፀሐፊ ነበር።በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ወጎችን የፃፈና ያሳተመ፤ ተርጓሚ፤ የሥነ-ፅሁፍ ሐያሲ እና አዲስ አበባና አሥመራ ዩኒቭርስቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ያስተማረ የሥነ-ፅሁፍ ሰዉ ነበር።መሥፍን በሕክምና ሲርዳ ቆይቶ ባለፈዉ ዕሁድ ነዉ ያረፈዉ።69 ዓመቱ ነበር።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር የቀብሩን ሥነ-ሥርዓት ተከታትሎት ነበር።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ