ደቡብ ሱዳን የፆታ ጥቃት
ሐሙስ፣ ግንቦት 11 2008ማስታወቂያ
የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ሐይላት ከጠላታቸዉ የወገነ ማሕበረሰብን ለማጥቃት የማሕበረሰቡን ሴቶችና ልጃገረዶችን መድፈር፤ ማገትና ማንገላታትን እንደ ወታደራዊ ሥልት መጠቀማቸዉን የመብት ተሟጋች ድርጅቶች አስታወቁ።አምንስቲ ኢንተርናሽናል ያስተባበራቸዉ ድርጅቶች ያደረጉት ጥናት እንዳመለከተዉ ደቡብ ሱዳን ዉስጥ ሴቶችና ልጃገረዶችን መድፈርና ማገት በጦርነቱ ወቅት አልቅጥ ቢባባስም ከጦርነቱ በፊትም በተደጋጋሚ ይፈፀም ነበር።በጥናቱ መሠረት ደቡብ ሱዳን ነፃነቷን ካወጀች ወዲሕ በተቆጠሩት አምስት ዓመታት ዉስጥ ከ10 ሺሕ በላይ ሴቶችና ልጃገረዶች ተደፍረዋል።ሥለ ጥናቱ ዉጤት የናይሮቢ ወኪላችንን በሥልክ አነጋግረነዉ ነበር።
ፋሲል ግርማ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ