1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ድርቅን የመቋቋሚያ ዘዴ በአፋር

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 25 2008

መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የኤልኒንዮ የአየር ፀባይ ለውጥን ተከትሎ ከፍተኛ ድርቅና እና ጎርፍ ያጠቃቸዉ አካባቢዎች ችግሩን በዘላቂነት ለመቋቋም በሚችሉበት ዘዴ ላይ እየሰሩ ይገኛሉ። ከነዚህ ድርጅቶች መካከል የጀርመኑ የቴክኒክ ተራእዶ ድርጅት «GIZ» «ቬልት ሁንገር ሂልፈ» እና የ«ጀርመን አግሮ አክሽን» ይገኙበታል።

https://p.dw.com/p/1Ih8i
Hilfsprojekten für die Opfer von Dürre und Flut in Afar
ምስል DW/G. Tedla

ድርቅን የመቋቋሚያ ዘዴ በአፋር

በዚሁ መሰረት በተነቃቁት ፕሮጀክቶች በአፋር ከሰመራ አዉራጃ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ሰርዶ አካባቢ ከሦስት መቶ በላይ የዝናብ ዉኃ ማቆርያ ጉድጓዶች ተሰርተዋል። በሰመራ አፋር ክልል የተፈጥሮ ኃብት ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ መሃመድ አህመድ እንደገለፁት፤ አርብቶ አደሩ ከብቱ በድርቅ ምክንያት እያለቀ ባለበት በአሁኑ ሠዓት ወላድ የሆኑ ፍየሎችና በጎችን ከማኃበረሰቡ እየገዛን ድርቁ ካለፈ በኋላ መልሰን ችግር ላይ ላለዉ አርብቶ አደር በስጦታ መልክ እንሰጣለን ሲሉ ተናግረዋል።

Hilfsprojekten für die Opfer von Dürre und Flut in Afar
ምስል DW/G. Tedla

ይህን ስንል አንደኛ አርብቶ አደሩ የቀንድ ከብቱ ከሚሞት ሸጦ ገንዘቡን ይጠቀምበታል፤ ሁለተኛ ማቆያ ስፍራ ላይ አስቀምጠን ድርቁ ሲያልፍ እንስሳቶቻቸዉን ላጡ እንደገና በስጦታ የምንሰጥበት ሂደት ነዉ ፤ «ዲስቶኪንግ» ና «ሪስቶኪንግ» ተብሎ ይጠራል ሲሉ አብራርተዋል።


ለሁለት ዓመታት ዝናብ ያልጣለበት የምስራቃዊ ኢትዮጵያ አፍር ግዛት ከፍተኛ ድርቅ መከሰቱ ይታወቃል። በአብዛኛዉ አርብቶ አደር በሚገኝበት በዚህ ክልል ያለዉ የቀንድ ከብት በዉኃ እጦት ምክንያት ከፍተኛ አደጋ ላይ መዉደቁም የሚታይ ሆንዋል። የአፋር ሕዝብ በባህሉ መሠረት ለቀንድ ከብት በሚሰጠዉ ከፍተኛ ግምት በዉኃ እጦት ድርቅ ላይ የወደቀዉን ከብት አርዶ የመብላት ፍላጎት እንደሌለዉ ይታወቃል። በአፍሪቃዉ ቀንድ በኢትዮጵያ በጅቡቲና በኤርትራ ወደ አራት ሚሊዮን አፋር እንደሚኖር ዘገባዎች ያሳያሉ።

Hilfsprojekten für die Opfer von Dürre und Flut in Afar
ምስል DW/G. Tedla

የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ ሰሞኑን አፋር አካባቢን ተዘዋዉሮ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከፍተኛ ድርቅና እና ጎርፍ ያጠቃቸዉ አካባቢዎች ችግሩን በዘላቂነት ለመቋቋም እያደረጉ ያሉትን ተመልካክቶ ሰፋ ያለ ዘገባ ልኮልናል።

ጌታቸዉ ተድላ ኃይለጊዮርጊስ

አርያም ተክሌ