1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጀርመናዊዉ ሄልሙት ሽሚድትና የኢትዮጵያዉያኑ አስተያየት

ሐሙስ፣ ኅዳር 9 2008
https://p.dw.com/p/1H98u


ባለፈዉ ሰሞን ከዚህ ዓለም በሞት እስከተለዩ ድረስ «ዲ ሳይት» በተሰኘ ጋዜጣ ላይ ተባባሪ አዘጋጅ በመሆን የሰሩት በጥሩ ተምሳሌነታቸዉ የሚታወቁት ጀርመናዊ የፖለቲካ ጉዳይ ተንታኝ ሄልሙት ሽሚድት በጀርመናዉያን ዘንድ ተወዳጅ ነበሩ። በጀርመን ረዘም ላለ ጊዜ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዉያንም ሄልሙት ሽሚድ በጀርመንነታቸዉ ብቻ ሳይሆኑ የሚገለፁት በጥሩ አዉሮጳዊነታቸዉ እንደሆነም ይመሰክሩላቸዋል በእለቱ ዝግጅታችን ባለፈዉ ሰሞን በ 96 ዓመታቸዉ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የጀርመን ፖለቲከኛ የሄልሙት ሽሚትድን ማንነት አንዳንድ ኢትዮጵያዉያንን አነጋግረን ይዘን ቀርበናል።