ጀርመን በአፍሪቃ ላይ የምትከተለዉ አመራር ዘይቤ
ማክሰኞ፣ መስከረም 11 2003ማስታወቂያ
ጀርመን በአፍሪቃ ባለፉት ጊዜያት ስታካሂድ የቆየችዉ ፖለቲካ የማይጨበጥ፤ ግራ የሚያጋባ፤ እርስ በርሱ የሚቃረን ነዉ። ይህን የሚያንፀባርቀዉ የአመራር ዘይቤዉ ረቂቅም በእጄ ይገኛል ሲል ማርኮስ ፍሬንዘል የተባለዉ የጀርመን የቴሌቪዥን ጋዜጠኛ ትችት ብቻ ሳይሆን በበርሊኑ ጣምራ መንግስትን ነቅፏል። ፍሬንዝል እንዳለዉ የጀርመን ፖለቲካ በአፍሪቃ ሰብዓዊ መብት ይከበር ይላል፤ በአንፃሩ ሰብዓዊ መብት ሲጣስ ሲረገጥ ዝም ብሎ አይቆ እንዳላየ ያልፈዋል። ጋዜጠናዉ ለዚህ ዋቢ ያደረገዉ ሶስት የአፍሪቃ አገሮችን ነዉ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ተክሌ የኋላ
ነጋሽ መሐመድ