1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጀርመን፤ የድንበር ቁጥጥር ልትጀምር ነው

እሑድ፣ መስከረም 2 2008

ጀርመን የስደተኞችን ቀውስ ተከትሎ ጊዜያዊ የድንበር ቁጥጥር ልትጀምር እንደሆነ «ቢልድ» የተሰኘው ጋዜጣ ዘገበ። እንደ ዘገባው ከሆነ ቁጥጥሩ የሚመለከተው የጀርመን እና የኦስትሪያ ድንበርን ይሆናል።

https://p.dw.com/p/1GVt4
Deutschland Österreich Grenze Polizei Flüchtlinge
ምስል picture-alliance/AP/M. Schrader

ጀርመን ድንበሯን ለስደተኞች ክፍት ካደረገች አንስቶ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ስደተኞች በኦስትሪያ በኩል አድርገው ጀርመን ገብተዋል። ትናንት ቅዳሜ እስከ እኩለ ሌሊት ብቻ 12,200 ስደተኞች ጀርመን ገብተዋል።በሌላ ዜና በወቅታዊው የስደተኛ ቀውስ ሳቢያ ከኦስትሪያ የሚደረጉ የባቡር ጉዞዎች በሙሉ ወደ ጀርመን መግባት ማቆማቸውን የኦስትሪያ የባቡር ድርጅት ቃል አቀባይ ዛሬ ማምሻውን አስታወቁ።

ልደት አበበ

እሸቴ በቀለ