1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ሐኪም ቤት ገባ-ቤተሰቦቹ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 18 2009

በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ረፋዱ ላይ ዝዋይ ባቱ ሐኪም ቤት እንደገባ የተመስገን ታናሽ ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ ለዶይቸ ቬለ ተናግሯል።

https://p.dw.com/p/2UvqV
Journalist Temesgen Desalegn
ምስል DW/Y. Geberegziabeher

MMT_Q&A-Temesgen Desalegen sei in Krankenhaus geliefert worden - MP3-Stereo

በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ዛሬ ረፋዱ ላይ ዝዋይ ባቱ ሐኪም ቤት እንደገባ ተሰምቷል። የተመስገን ታናሽ ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ ለዶይቸ ቬለ ዛሬ እንደገለፀዉ  ጋዜጠኛ ተመስገን በምን ኹኔታ ላይ እንዳለ ለማወቅ ወደ ሐኪም ቤቱ ሄደው ቢጠይቁም መግባት እንደተከለከሉ ገልጧል።

ታሪኩ ጋዜጠኛ ተመስገንን ካለፉት ዐሥር ቀናት አንስቶ ማየት እንዳልቻሉ፥ በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝም እንደማያውቁ  አስታውቋል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይገኝበታል የተባለው የባቱ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ ኑራ ነገዎ «እንደዛ የሚባል ሰው እኛ ጋ አልገባም» ሲሉ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል። 
 

ማንተጋፍቶት ስለሺ

አዜብ ታደሰ