ግጭት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 25 2005ማስታወቂያ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ4 ኪሎ ቅፅር ግቢ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት ተማሪዎች መጎዳታቸውና በግጭቱ የተጠረጠሩም መያዛቸው ተስምቷል ። ከትናንት ከሰአት በኋላ አንስቶ እስከ ዛሬ ጠዋት በቀጠለው ግጭት ተማሪዎች እንደቆሰሉና በተማሪዎች መኝታ ክፍሎች ላይም ጉዳት መድረሱን የአይን ምስክሮች መናገራቸውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ገልጾልናል ። አካባቢውም በፌደራል ፖሊስ ይጠበቅ እንደነበረም ተነግሯል ። ስለ ሁኔታው የአዲስ አበባውን ዘጋቢያችንን ዮሐንስ ገብረ እግዚ አብሔርን በስልክ አነጋግረናል።
ዮሐንስ ገብረ እግዚ አብሔር
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ