ጥንታዊ የድንጋይ ቅርጽና ተፈጥሮዋዊ ሃብት በጌዶ ዞን
ዓርብ፣ ኅዳር 13 2000ማስታወቂያ
የጌዶ ዞን መልካ-ምድራዊ አቀማመጥ የተለያየ የአየር ጸባይ ቢታይም በአብዛኛዉ የወይና ደጋማ እንደሆነ ጹሁፎች ያሳያሉ። ከአዲስ አበባ 395 ኪሎሜትር ርቃ የምትገኘዋ ይርጋ ጨፊ ከተማ እና አካባቢዋ አለምን በአስደመመዉ የቡና እና የእንሰት ምርት ታዋቂ አድርጓታል። ጌዶ ዞን ተፈጥሮ ከለገሰዉ የተለያየ አዝርት እና እፀዋት ሌላ ከድንጋይ የተፈለፈለ የሰዉ አካል ቅርጽን የያዘ ጥንታዉ የተክል ድንጋይ ቅርጻ ቅርጽም ይገኛል። የአካባቢዉ ተጠሪዎች ይህንን የተለየያየ የእጽዋት ሃብት እና ጥንታዊ ቅርጻ ቅርጽ ሃብት፣ በአለም ቅርጽነት እንዲመዘገብ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ።። በቅርቡ በተካሄደዉ የባህላዊዉ ምግብ ዉድድር የጌዶ ዞን ከቆጮ የተሰሩ የተለያዩ ምግቦችን በማቅረብ አንደኛነትን አግኝቷል።